12/05/2021
ዛሬ ማምሻውን አስራኤል ፍልስጤም ጋዛ ውስጥ የሚገኝ ባለ 13 ፎ ህንፃ በሚሳኤል መታ ማውደሟ ተነገረ‼️
በምስራቅ እየሩሳሌም የሚገኙ ፍልስጤማውያንን እስራኤል ማስወጣቷን ተከትሎ በሁለቱ ወገኖችበኩል ያለው ፀብ እየተካረረ የመጣ ሲሆን ዛሬ ማክሰኞ ምሽት 1:30 ገደማ በፍልስጤሟ ጋዛ ከተማ የሚገኘው ባለ 13 ፎቁ ሀናዲ የመኖርያ ህንፃ በእስራኤል የጦር አውሮፕላኖች በተተኮሰ ሚሳኤል መውደሙ የተነገረ ሲሆን ህንፃው ውስጥ የሚኖሩ ነዋሪዎች ቀድመው አንዲወጡ እስራኤል አስጠንቅቃ ነበር ሲል ጂውሽ ፕሬስ ዘግቧል።
ከህንፃው መውደም ጋር ተያይዞ እስከ አሁን በሰው ዘንድ የደረሰ ጉዳት ሪፖርት አልተደረገም።