06/04/2026
*የ97ቱ የክህደት መምህር!*
የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመጀመሪያ ጊዜ በነቂስ ወጥቶ የዴሞክራሲ ተስፋን ሰንቆ በነበረበት የ1997ቱ ምርጫ፣ ያንን ታላቅ የሕዝብ አደራና ድምፅ በጠራራ ፀሐይ የሸጠ ግለሰብ ቢኖር ልደቱ አያሌው ነው።
- የቅንጅት መፍረስ፦ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ሕዝብ የተመካበትን ቅንጅትን ከውስጥ በመናድ፣ የወያኔ ተላላኪ በመሆንና የሕዝብን ድምፅ ለግል ጥቅሙ በመለወጥ ረገድ ልደቱ አቻ የለውም።
- የሦስተኛው መንገድ ቁማር፦ ሁልጊዜም "ሦስተኛ መንገድ" እያለ የሚያወራው፣ ሀገር በጭንቅ ውስጥ ባለችበት ሰዓት መሃል ላይ ቆሞ የራሱን የፖለቲካ ትርፍ ለመሰብሰብና መንግስት በፈለገው ጊዜ "ሪዘርቭ" ተጫዋች ሆኖ እንዲያገለግል ነው። ዛሬም የሚሰጠው "ትውልዱን እናድን" ባይ ትንታኔዎች፣ ያንን የድሮውን ክህደት በዘመናዊ ቃላት ለመሸፈን የሚደረግ ከንቱ ጥረት ነው።