HALAL Promotions

HALAL Promotions Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from HALAL Promotions, Event Planner, Piassa, Country Tower, 4th floor, Addis Ababa.

ሀገር አቀፍ የቁርኣን ሂፍዝ ውድድርበታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር - 5ቁርኣን የእውቀትና የሰላም ምንጭመጋቢት 7-2017
15/03/2025

ሀገር አቀፍ የቁርኣን ሂፍዝ ውድድር
በታላቁ የጎዳና ላይ ኢፍጣር - 5
ቁርኣን የእውቀትና የሰላም ምንጭ
መጋቢት 7-2017

- የተለመደውን ለጸጥታ አካላት እና ለበጎ ፍቃድ አስተባባሪዎች ፍተሻ ትብብር ማድረግ- የሰላት መስገጃ እና ጥላ ይዘው ይምጡ- ማንኛውም ለደህንንት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፍቃደኛ...
15/03/2025

- የተለመደውን ለጸጥታ አካላት እና ለበጎ ፍቃድ አስተባባሪዎች ፍተሻ ትብብር ማድረግ
- የሰላት መስገጃ እና ጥላ ይዘው ይምጡ
- ማንኛውም ለደህንንት አጠራጣሪ ሁኔታዎች ከተመለከቱ ለበጎ ፍቃደኛ አስተባባሪዎችና ለጸጥታ አካላት በአፋጣኝ እንዲያሳውቁ
- የ CAR PASS ያላቸው ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ የዝግጅቱ ታዳሚያን ጊዮን ሆቴል ጊቢ ውስጥ እና እስታዲይም አካባቢ መኪና እንዲያቆሙ።
- የ CAR PASS ካላቸው እንግዶች ውጭ ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ የዝግጅቱ ታዳሚያን በአቅራቢያ ባሉ በኮሪደር ልማቱ በተሰሩ አልያም ሌሎች ምቹ በሆኑ ስፍራዎች መኪና እንዲያቆሙ።
- ለማፍጠሪያ የሚሆንና ከሙስሊም እህትና ወንድሞቻች በማካፈል ኢፍጣርን ለሌሎች በማጋርት የሚገኘውን አጅር ተቋዳሽ እንዲሆኑ ጥሪ እናደርጋለን፡፡ ምግቦቹ እንደ ቴምር፣ ውሃ እና የታሸጉ ምግቦች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ከፕሮግራሙ አላማ ውጭ ማንኛውም ተግባር ተቀባይነት የሌለው መሆኑ
- በከተማችን የትራንስፖርት ችግር መኖሩ የሚታወቅ በመሆኑ የግል ተሽከርካሪ ይዘው የሚመጡ የዝግጅቱ ታዳሚያን ፆመኞችን ወደ ዝግጅቱ ሲመጡ እና ሲመለሱ የትራንስፖርት አገልግሎት በ መስጠት ትብብር ቢያደርጉ።
- ለኢፍጣር የተዘጋጁ ምግቦችን ከመብልነት ውጭ መጠጦችን ከመጠጥነት ውጭ በመጠቀም ማባካን እና ከዝግጅቱ ዓላማ ውጪ ከሆኑ ድርጊቶች በመቆጠብ ኢስላማዊ ስነምግባራችንን ለሌሎች ዓርኣያ በመሆን ማሳየት

የአንድ ብዙየሥነ ምግባር ምሉዕነት ለረሱል (ሰዐወ) የተገባ ነው። አቡበከር ሲዲቅ ደግሞ የእሳቸው የቅርብ ሰው ናቸው። ረሱል (ሰዐወ) "ኢንነማ ቡዒስቱ ሊዑተሚመ መካሪመል አኽላቅ" ማለታቸውን...
28/03/2024

የአንድ ብዙ

የሥነ ምግባር ምሉዕነት ለረሱል (ሰዐወ) የተገባ ነው። አቡበከር ሲዲቅ ደግሞ የእሳቸው የቅርብ ሰው ናቸው። ረሱል (ሰዐወ) "ኢንነማ ቡዒስቱ ሊዑተሚመ መካሪመል አኽላቅ" ማለታቸውን ስናስብ የአንድ ሰውን ያህል በእርግጥ እኛ ሰምተን ታንጸናል ወይ? ብለን ራሳችንን እንድንጠይቅ ያደርገናል።

አንዳንድ ሰዎች አሉ ጆሯቸው ሰምቶ የማይሞላ፣ ሞልቶም የማያፈስ። ሁሉንም ዓይነት ድምጽ በጥሞና ሰምቶ ተገቢውን ምላሽ የመስጠት አቅም ያላቸው። እነሱን መሆን አይቻልም። እነሱን መሆን የሚችሉት እነሱ ብቻ ናቸው።

እያንዳንዱ ሰው የየራሱ መክሊት አለው። በጥበብ ሜዳ ላይ የሚጎን፣ በሃብት ሜዳ ላይ የሚገን፣ ለንግግር አንደበቱ ስል፣ ለፈጠራ ምናቡ ሩቅ፣ የሆነ ሰው አለ። እያንዳንዱ ሰው የየራሱ መክሊት አለው። ለአንዳንድ ሰው ደግሞ የተነባበረን አላህ ይሰጠዋል።

መከራን የሚቋቋም ትከሻ፣ ጡጫን የሚመክት ሰውነት፣ ግለምጫን የሚቋቋም ክብር፣ ችግርን የሚሻገር ጉልበት፣ አመራርነትን የተካነ ምጥቀት በአንድ ሰው ላይ ይታይ ይሆናል። የአንድ ብዙ።

በመልዕክተኛው የሥነምግባር አስተምህሮ ታንጾ በመጀመሪያው ኸሊፋ ምሉዕ ጠባይ ተኮትኩቶ ያደገ የዘመናችን ተምሳሌት ደግሞ መሐላችን አለ።

ትሕትና ሥጋ ለብሶ፣ ኃላፊነት ግዘፍ ነስቶ የሚታይበት የዘመናችን አርዓያ ሰብ። ነገሮች ቢያበሳጩት ውጦ፣ ንዴቱን ተቆጣጥሮ የዕለት ተግባሩን የዓመት ውጤቱን የሚያሰላ የትውልዱ አርዓያ ሰብ።

ሥነምግባርንም ከሲዲቅ ተውሷል። ባሕሪንም አስተምህሮንም ከረሱል ሰዐወ ድርሳነ ማኅደር አፍሷል። ይህ ሰው የዘመናችን ድንቅ ሆኖ ሳለ መሐላችን በመኖሩ አላወቅንለትም።

ከግለሰብ እስከ አገር ጉዳይ ይዞ ከቆላ ደጋ ሲባትል መች ይሆን የራሱን ሕይወት የሚኖር ያስብላል።

ትናንት መቀሌ ከነበር ነገ ሞያሌ ሊገኝ ይችላል፣ ጅግጅጋ ነው ሲሉት ባሌ ሮቤ ይታያል። ኢትዮጵያ ነው ሲሉት አሜሪካ፥ አሜሪካ ነው ሲሉት ዱባይ፣ ዱባይ ነው ሲሉት ካናዳ፣ ካናዳ ነው ሲሉት ቱርክ፣ ጣሊያን ፣ ጀርመን .... እሱ እዚህ ነው ብለው ሊደመድሙ አይችሉም። ይህ ሁሉ ታዲያ ለግል ጉዳዩ አይደለም።

አንዱ ጋ ሕዝቡን ከአላህ ጋር ያስታርቃል ፣ ሌላው ጋ የሕዝባችን ዋእይና ቸነፈር በዝቷልና እጃችሁን ወደኪሳችሁ ከትተታችሁ ሳትሰስቱ አምጡ ይላል። የሕዳሴው ግድብን ከእናንተ ውጪ የሚያጠናቅቀው የለም አምጡ፣ የኮረናን መከራ የምንቋቋመው በእናንተው ነው አምጡ እያለ አንድ ሆኖ ሺ ቦታ ይደርሳል። ኢትዮጵያ የዚህን ሰው ታላቅነት አለማወቋ የሚገርም ነው። በጎ ነው ብላ አልሸለመችው ደግ ነው ብላ አላወቀችው።

ቃል ሲገባ ካዝናው ውስጥ ያለውን አሟጦ ነው። ሲሰጥ ከነገውም ይበደራል። ምነዋ ቢሉ ከፊቱ የቆመው ችግር ውሎ የማያሳድር ይሆንበታል። ቢበዛልን የምንወደው ስናጣው የሚከፋን የዘመናችን ወደረኛ አልባ።

የእከሌ ወገን ተብሎ የማይመደብ፣ የቡድንተኝነት ማልያን የማያጠልቅ፣ ለተቸገሩ መሻኢኾች፣ ለተዘጉ ዛውያዎች፣ ለፈረሱ መሳጂዶች፣ ለወደቁ ስብእናዎች ሁሉ የሚጠራ የዘመኑ አርዓያ ሰብ። ችግር ባለበት ሁሉ አባ መፍትሔ።

መች ይሆን ለራሱ የሚኖረው? በሌሊት በኦንላይን ለአንዱ ተቋም ገቢ ሲያስብ ያገኙታል፥ በእኩል ቀን "ስንቅ ማጋራት" ሲያስተባብር ያዩታል። የጎዳና ወጣቶችን ለማብላት ይሮጣል፣ ችግኝ ለመትከል አፈር ይዝቃል። ሕመምተኞችን ሆስፒታል ሄዶ፣ ቁስለኞችን ግምባር ተገኝቶ ያጽናናል። ይህን ሰው ምን ብለን ብንገልጸው ይበቃው ይሆን?

የራሱ ሳይበቃ ቤተሰቦቹንም በራሱ መንገድ ያሰለፈ፣ ከሕመሙ ጋ ተናንቆ አደባባይ በአገር ጉዳይ፣ በዑማ ጉዳይ የሚጋፈጥ ምርጥ ሰብዕና።
የሕዝብ ድምጽ፣ የዑማው ልሳን፣ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ማነው?

ዑስታዝ አቡበከር አሕመድ ሐላል ፕሮሞሽን በ4ኛው የጎዳና ላይ ኢፍጣር የኢትዮጵያ ኡስታዝ አቡበከር አህመድን የክብር እውቅና ይሸልማል።

ይህ ሽልማት የሕዝብ ነው። ሕዝብ ልጁን ያከብራል

እንግዶቻችንን ለመቀበል ዝግጅታችንን ጨርሰናል::ታላቁ የጎዳና ላይ ዒፍጣር 4መጋቢት 18.   2016
27/03/2024

እንግዶቻችንን ለመቀበል ዝግጅታችንን ጨርሰናል::
ታላቁ የጎዳና ላይ ዒፍጣር 4
መጋቢት 18. 2016

ዝግጅቱ እንደቀጠለ ነው!ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ 4መጋቢት 18/2016
26/03/2024

ዝግጅቱ እንደቀጠለ ነው!
ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር በኢትዮጵያ 4
መጋቢት 18/2016

26/03/2024

በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚካሄደው የአደባባይ ላይ የኢፍጥር ፕሮግራም በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጀት ማጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ሐይሉ አስታወቀ ፡፡ በነገው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርኃ ግብር ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡
***
በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚካሄደው የአደባባይ ላይ የኢፍጥር ፕሮግራም በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጀት ማጠናቀቁን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ሐይሉ አስታውቆ በፕሮግራሙ አከባበር ዙሪያ ከእምነቱ አባቶችና ከወጣት በጎ ፈቃደኞች ጋር ተገቢውን ውይይት በማድረግ ዝግጅት መደረጉንም ግብረ-ሐይሉ ገልጿል፡፡ የእምነቱ ተከታዮች ወደ ኢፍጥር ፕሮግራሙ ሲመጡ ለጋራ ደህንነት ሲባል ፍተሻ መኖሩን ተረድተው እንደወትሮው ሁሉ ትብብር እንዲያደርጉ የተጠየቀ ሲሆን ከፕሮግራሙ ጋር የማይሔዱ በህግ የተከለከሉ እና ስለታማ ነገሮችን ይዞ መምጣት ፈፅሞ ክልክል መሆኑን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሐይሉ አስታውቋል፡፡
በነገው ዕለት መጋቢት 18 ቀን 2016ዓ.ም በአዲስ አበባ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርኃ ግብር ጋር ተያይዞ ከ5፡00 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም መሰረት፡-
• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅ/ኡራኤል ቤ/ክርስቲያን
• ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ
• ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ለከባድ መኪናዎች አጎና ሲኒማ፤ለሌሎች ተሸከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡
• ከጦር ኃይሎች በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሸከርካሪዎች በተለምዶ አጠራሩ ክቡ ባንክ አካባቢ፡፡
• ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ሐራምቤ መብራት ላይ፡፡
• እንዲሁም ከ4 ኪሎ በውጭ ጉዳይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛው ላይ፡፡
• ከአዋሬ አካባቢ በካሳንቺስ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ኢንተርኮንትኔታል አካባቢ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጠር ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅበት ሰዓት ድረስ ዝግ የሚደረጉ ይሆናል፡፡
በተጨማሪም በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅመ ሰዓታት ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ የተከለከለ ሲሆን ኅብረተሰቡ መርኃ ግብሩ በሠላም ተጀምሮ በሠላም እንዲጠናቀቅ ለፀጥታ አካላት ተባባሪ እንዲሆንና ማንኛውም ዓይነት አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ በፖሊስ የመረጃ ስልኮች 0111 11 01 11 እና ነፃ የስልክ መስመር 991 ላይ በመደወልና መረጃ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ የፀጥታና የደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል አስታውቋል፡፡

Address

Piassa, Country Tower, 4th Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when HALAL Promotions posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to HALAL Promotions:

Share

Category