R50rrmhfiuv

R50rrmhfiuv Consultancy service

19/04/2025

የጴጥሮስ ዶሮ (ወንጌል ሰባኪ)

ከሐዋርያቱ መካከል በዕድሜው አንጋፋ ክርስቶስ ሲጠራው 55 ዓመት የነበረው፣በወንድሙ እንድርያስ አማካኝነት ወደ ጌታ የቀረበ፣
ለክርስቶስ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ፣
አረጋዊ ቅን የሆነ ፍፁም ትሁት ሐዋርያ፣
አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ የመሰከረ፣
ከሐዋርያቱ የመጀመሪያው ለአህዛብ ወንጌልን የሰበከ፣
ለክርስቶስ ካለው ፍፁም ፍቅር የተነሳ ጌታ እሞታለሁ ሲላቸው አይሁንብህ፣በማለት የተከራከረ ጌታችንም የገሰፀው፣ከወንድሞቹ ሐዋርያት ጋር ሆኖ ዓለምን በወንጌል ያበራ፣
የሐዋርያት አለቃቸው፣የቤተክርስቲያን ዓለት ነህ በአንተ ላይ ቤተክርስቲያን ትሰራለች የተባለው።
ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችን መድሃኒታችን በተያዘ ሌሊት በዚያ የመከራ ሰዓት፣
ከመከራው ፅናት የተነሳ ሌሊቱ ረጅም በሆነበት ወቅት፣ሌሎቹ ሐዋርያት በጌታ መያዝ ወዲያና ወዲህ በተበታተኑበት ሰዓት፣ይሁዳ ከአይሁድ የወሰደውን ሠላሳ ዲናር በሚቆጥርበት ሌሊት፣
ማርቆስ አይሁድ ሲይዙት የለበሰውን ነጠላ እጃቸው ላይ፡ጥሎ ዕርቃኑን ሲፈረጥጥ፣
እናቱ ድንግል ማርያም የሃዘን ሰይፍ ነፍሷን ሲያሰቃያት፣
እነማርያም መግደላዊት በፍርሃትና ረዓድ ሆነው ሲጨነቁ፣
ዮሐንስ ፊቱ በሃዘን ሲጠቁር ሲያለቅስ ።

በዚያ አስጨናቂ ሌሊት የአይሁድ ወታደሮች ወይን እየጡጡ ሲሳሳቁ፣
በክርስቶስ ጀርባ አለንጋ ሲወርድ፣
ንጉስ ሆይ ሺህ ዓመት ንገስ በማለት የእሾህ አክሊል እያደረጉለት ሲዘባበቱ፣ለህይወት ውሃ ውሃ ሲከለክሉት፣

ጴጥሮስ ከአይሁዳውያኑ መሃል ሆኖ እሳት እየሞቀ አይተንሃል ከእርሱ ጋር ነበርክ፤የእርሱ ደቀመዝሙር ነህ ፣ከእርሱ ወገን ነህ፣
ንግግርህ ይመሰክራል ሲባል የምትሉትን አላውቅም ።
በማለት ዶሮ አንዴ ሳይጮኽ ሦስቴ ካደው።
ከሦስት ክህደት በዃላ ዶሮ አንዴ ጮኸ፡፡ጴጥሮስም ያኔ ነቃ ፤የጌታው ቃል ትዝ አለው።
ተፀፀተ አለቀሰ አብዝቶ አነባ ፍቅር የሆነው አምላክ ኢየሱስም ፀፀቱን ተቀብሎ እንባውን መዝኖ የበለጠ ሾመው የበለጠ አከበረው የበለጠ ወደደው።
ግን ያ ዶሮ በአንድ ጩኸት ጴጥሮስን ያነቃ ያ ዶሮ ምን አይነት ዶሮ ይሆን? ምንስ አይነት ጩኸት ምንስ ዓይነት ስብከት ነው ያሰማው?
የጴጥሮስስ ልብ እንዴት ያለው ቅን ልብ ነው?የተዘጋጀ ለንሰሃ ቅርብ የሆነ አምላኩን የሚወድ እንደ ይሁዳ ያልጠመመ፣
እንደ ፈርዖንም ያልደነደነ
መልካም እርሻ የሆነ እንዴት የተባረከ ልብ ነው?ዛሬ በየቤተክርስቲያኑ ብዙዎች እንደዶሮው እንጮኻለን፣
ሰሚ የለም፣ምክንያቱም ጩኸታችን የማስመሰል ራስን የመስበክ ዝና ፍለጋ ነውና።
ጩኸታችን የቁራ ጩኸት ነው።
ሰሚየሌለው እንደ ጴጥሮስ ለንሰሃ ሳይሆን የተዘጋና የተቆለፈ ልብ ይዘን ስለሐጢዓታችን ንሰሃ ሳንገባ ስንት ሌሊት ስንት ቀናት አለፉ ።
ዶሮዎቹ ወይም ሰባክያኑ ስለአጯጯኻቸው (ስለስብከታቸው) ቃላት መረጣ እና ፕሮቶኮል ሲጨነቁ፣
ሰሚዎቹም (ምዕመናኑ)በዶሮዎቹ /በሰባክያኑ/ጩኸት ሲደነቁ ብዙ ዘመናት አለፉ፡፡
ጌታሆይ እንደ ጴጥሮስ ቅን ልቦና፣እንደ
ዶሮዉም ለንሰሃ የሚያበቃ አገልጋይ ስጠን።

የሞቱትን ነፍስ በአጸደ ገነት ያሳርፍ።
01/04/2025

የሞቱትን ነፍስ በአጸደ ገነት ያሳርፍ።

Logical and recomended principle for others
01/04/2025

Logical and recomended principle for others

ህይወትን የምትሰጥ እናት ለሆስፒታል ለምን ትከፍላለች? ትራኦሬ‼️

በቡርኪኒፋሶ ከዛሬ ጀምሮ በሁሉም የመንግስት ሆስፒታል ሴቶች ያለምንም ክፍያ በነፃ ልጅ እንዲወልዱ ተወስኗል።

"እኔ የተወለድኩት ከሴት ልጅ ነው ሴት ልጅ ህይወትን ወደ እዚች ምድር ለማምጣት ብዙ ክፍያ ስትጠየቅ ማየት አልፈልግም ።
ድሃ እናቴ እኔን ለመውለድ በሚከፈል ክፍያ ምክንያት እኔን ልታጣ ነበር። ፈጣሪ ባይፈቅድ ኖሮ እኔም በህይወት የለሁም ነበር:: ዛሬ የዚህች አገር ፕሬዚዳንትም አልሆንም ነበር። ስለዚህ ህይወትን የምትሰጥ እናት ለሆስፒታል መክፈል የለባትም።"
የብርኪናፋሶ ፕሬዝደንት ኢብራሂም ትራኦሬ

29/03/2025

# # # # # # ራስ አበበ አረጋይ # # # #
(በፈረስ ስማቸው አባ ገስጥ)

በ፲፰፻፺፮ ዓ.ም በነሀሴ ፲፬ቀን በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት ውስጥ ተወለዱ። የቤተክርስቲያንና ዘመናዊ ትምህርት ተከታትለዋል፤ የክቡር ዘበኛ ሰራዊት አባል ሆነው ሚሊታሪ ሳይንስ በማጥናት በመጀመሪያ የሌተናንት ቀጥሎም የካፕቴንነት ማዕረጎችን ተቀብለዋል። ራስ አበበ አረጋይ በ1928 ዓ. ም ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ሲወር የአዲስ አባባ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ነበሩ።
በወቅቱ ፋሽስት ኢጣሊያ ከ40 ዓመት በፊት አድዋ ላይ በኢትዮጵያውያን የደረሰባትን አሳፋሪ ሽንፈት ለመበቀል በማይጨው ጦርነት ላይ የተጠቀመቸው በአውሮፕላን የሚረጭ የመርዝ ጋዝ በመሆኑና ከጠላት ጋር አብረው የነበሩት ባንዳዎች ለጣልያን የኢትዮጵያን ምስጢር ይሰጡ ስለነበር በጦርነቱ የወገን ጦር ክፉኛ በመጎዳቱ ንጉሱን ጨምሮ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ግድ ሆነ። ከማይጨው ጦርነት በኋላ ጠቅላላ ወታደሩ ወደ ሽምቅ ውጊያ ለመግባት ተገደደ። ራስ አበበ አረጋይ የኢትዮጵያን የነፃነት ሰንደቅ ዓላማ አንግበው አምስት ዓመት ሙሉ በሰሜን ሸዋ (በዱር በገደል)የኢትዮጵያን ሽምቅ ተዋጊዎች በመምራትና የጣሊያን ወራሪ ኃይል አሳፍረው በመመለስ ትልቅ ጀብዱ ፈጽመዋል። ከአምስት ዓመት አርበኝነት ተጋድሎ በኋላ የፋሽስቱ ወራሪ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተጠራርጎ ከኢትዮጵያ ለቋል።

(ከዝክረ ሚያዝያ ፳፯ በፌስቡክ)

23/03/2025

1647 followers, 639 likes, 28 comments

ታሪክን የኋሊት እንበለው
19/03/2025

ታሪክን የኋሊት እንበለው

▼ኮሎኔል አጥናፉ አባተ

#ኮ/ል መንግሥቱ ደርግን ኮትኩተው አሳድገውት ይሆናል። ነገር ግን አልወለዱትም። የደርግ እናትም አባትም ኮ/ል አጥናፉ ናቸው። ኾኖም ደርግ ፈጣሪውን መልሶ ለመብላት የወሰደበት ጊዜ ከ5 ዓመት ያነሰ ነበር፡፡ ኅዳር 3/ 1970 በዕለተ ቅዳሜ አጥናፉ ተገደሉ። "አብዮት ልጆቿን በላች" ተባለ።

#ሲያልቅ አያምር ሆኖ እንጂ መንጌና አጥናፉ ጎረቤት ነበሩ። ሚስቶቻቸው ውባንቺና አስናቀች በአንድ ስኒ ቡና ጠጥተዋል። ትምህርትና ትዕግስት ከነሱራፌል አጥናፉ ጋር ኳስ ሲራገጡ፣ መሐረቤን ያያችሁ ሲጫወቱ ይውሉ ነበር። ጨርቆስ፣ መሿለኪያ፣ 4ኛ ክፍለ ጦር ግቢ የሟችም የ'ገዳይ'ም ቤት ነበር።

#መንጌ ቀኝ እጃቸው፣ ጎረቤታቸውና ለአጭር ጊዜም ቢሆን አለቃቸው በነበሩት ሻለቃ አጥናፉ ላይ ድንገት "ሲጨክኑ" ሐዘኑ ከባድ ሆነ። የሟች ልጅ ሱራፌል አጥናፉ እንደሚያስታውሰው ከሆነ ገራገሯ ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ለቅሶ ደርሰዋቸዋል። "ትዝ ይለኛል እማዬ ወይዘሮ ዉባንቺን 'ባልሽ ባሌን ገደለው!' እያለቻት ተቃቅፈው ሲላቀሱ" ይላል ሱራፌል።

#ለመሆኑ ከኮሎኔል አጥናፉ አባተ መገደል በኋላ ልጆቹ እንደምን ኖሩ? ከ8ቱ ልጆች 5ኛው ሱራፌል አጥናፉ "መንጌ አባቴን ካስገደለ በኋላ እኛን እንዳሮጌ ዕቃ ከቤት አውጥተው ጣሉን..." ሲል ረዥሙን ቤተሰባዊ ምስቅልቅ በአጭር ዐረፍተ ነገር ይጀምራል፡፡

"ሁለቱ ወንድሞቼ በብስጭት ሞቱ"

#ሱራፌል አጥናፉ አባተ እባላለሁ። የኮ/ል አጥናፉ 5ኛ ልጅ ነኝ። አሁን እኔ ራሴ አምስት ልጆች አሉኝ። የምተዳደረው በሹፍርና ነው።

#የአጥናፉ ልጆች 8 ነን። አሁን በሕይወት ያለነው ግን አምስት ስንሆን ሦስቱ በሕይወት የሉም። የሁለቱ ሞት ከአባታችን መገደል ጋር የተያያዘ ነው። አባታችን አጥናፉ የተገደለው ሁለቱ ወንድሞቼ ራሺያ በሄዱ ልክ በ10ኛው ቀን ነበር።የታላቄ ታላቅ ሰለሞን አጥናፉ ይባላል። ራሺያ ለከፍተኛ ትምህርት እንደሄደ ያባታችንን ሞት ሲሰማ በዚያው የአእምሮ በሽተኛ ሆነ። እዚህ መጥቶ አማኑኤል ሆስፒታል ተሞከረ፤ አልተቻለም። እናታችን ብዙ ደከመች። አልሆነም።

#በጣም ይበሳጭ ነበር፤ በአባታችን ሞት። ለምሳሌ እንደማስታውሰው ድንገት ተነስቶ በእግሩ ጎጃም ድረስ ይሄድ ነበር። አእምሮው ታወከና በመጨረሻ ብዙም አልቆየ ራሱን አጠፋ።

#የሁላችንም ታላቅ ዶክተር መክብብ አጥናፉ ይባላል። እሱም እንዲሁ በአባታችን አላግባብ መገደል በጣም ይበሳጭ ነበር። ራሺያ ሕክምና ተምሮ ከተመለሰ በኋላ ብዙ ዓመት ሆሳዕና "መንግሥቱ ኃይለማርያም ሆስፒታል" ሠርቷል። አባቱን በገደለው ሰው ስም በተሰየመ ሆስፒታል ውስጥ መሥራት ምን ስሜት እንደሚሰጥ አስበው።

#ከሆሳዕና ሕዝብ ዶክተር መክብብን የማያውቅ የለም ማለት ይቻላል። ተወዳጅ ሐኪም ነበር። ግን በአባታችን ሞት እጅጉኑ ይበሳጭ ነበር። እኔ እጨቃጨቀው ነበር።

'በቃ አባታችን የሚያምንበትን ሠርቶ አልፏል። እኛ የራሳችንን ሕይወት ነው መኖር ያለብን' እለው ነበር። እሱ ግን ብዙ ምስጢር ያውቅ ስለነበር አይሰማኝም፤ በጣም ብስጩ ሆነ። በመጨረሻ እሱም ጭንቅላቱ ተነካና ሞተ።

#ሟች ወንድሞቻችን ሰለሞንና ዶክተር መክብብ አባታችን ነገሌ፣ 4ኛ ክፍለ ጦር እያለ የተወለዱ ነበሩ። ሌሎቻችን ግን እዚህ መሿለኪያ 4ኛ ክፍለ ጦር ግቢ ውስጥ ነው የተወለድነው። ቴድሮስ፣ ጌታሁን፣ ሳምሶን፣ እንዳለ፣ እህታችን አብነት፣ እኔን ጨምሮ- ሁላችንም የመሿለኪያ ልጆች ነን፡፡

◈ምንጭ -BBCNewsAmharic



17/03/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ

16/03/2025

15.9K likes, 119 comments. “ ”

06/03/2025
05/03/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when R50rrmhfiuv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share