R50rrmhfiuv

R50rrmhfiuv Consultancy service

19/04/2025

የጴጥሮስ ዶሮ (ወንጌል ሰባኪ)

ከሐዋርያቱ መካከል በዕድሜው አንጋፋ ክርስቶስ ሲጠራው 55 ዓመት የነበረው፣በወንድሙ እንድርያስ አማካኝነት ወደ ጌታ የቀረበ፣
ለክርስቶስ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ፣
አረጋዊ ቅን የሆነ ፍፁም ትሁት ሐዋርያ፣
አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ የመሰከረ፣
ከሐዋርያቱ የመጀመሪያው ለአህዛብ ወንጌልን የሰበከ፣
ለክርስቶስ ካለው ፍፁም ፍቅር የተነሳ ጌታ እሞታለሁ ሲላቸው አይሁንብህ፣በማለት የተከራከረ ጌታችንም የገሰፀው፣ከወንድሞቹ ሐዋርያት ጋር ሆኖ ዓለምን በወንጌል ያበራ፣
የሐዋርያት አለቃቸው፣የቤተክርስቲያን ዓለት ነህ በአንተ ላይ ቤተክርስቲያን ትሰራለች የተባለው።
ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታችን መድሃኒታችን በተያዘ ሌሊት በዚያ የመከራ ሰዓት፣
ከመከራው ፅናት የተነሳ ሌሊቱ ረጅም በሆነበት ወቅት፣ሌሎቹ ሐዋርያት በጌታ መያዝ ወዲያና ወዲህ በተበታተኑበት ሰዓት፣ይሁዳ ከአይሁድ የወሰደውን ሠላሳ ዲናር በሚቆጥርበት ሌሊት፣
ማርቆስ አይሁድ ሲይዙት የለበሰውን ነጠላ እጃቸው ላይ፡ጥሎ ዕርቃኑን ሲፈረጥጥ፣
እናቱ ድንግል ማርያም የሃዘን ሰይፍ ነፍሷን ሲያሰቃያት፣
እነማርያም መግደላዊት በፍርሃትና ረዓድ ሆነው ሲጨነቁ፣
ዮሐንስ ፊቱ በሃዘን ሲጠቁር ሲያለቅስ ።

በዚያ አስጨናቂ ሌሊት የአይሁድ ወታደሮች ወይን እየጡጡ ሲሳሳቁ፣
በክርስቶስ ጀርባ አለንጋ ሲወርድ፣
ንጉስ ሆይ ሺህ ዓመት ንገስ በማለት የእሾህ አክሊል እያደረጉለት ሲዘባበቱ፣ለህይወት ውሃ ውሃ ሲከለክሉት፣

ጴጥሮስ ከአይሁዳውያኑ መሃል ሆኖ እሳት እየሞቀ አይተንሃል ከእርሱ ጋር ነበርክ፤የእርሱ ደቀመዝሙር ነህ ፣ከእርሱ ወገን ነህ፣
ንግግርህ ይመሰክራል ሲባል የምትሉትን አላውቅም ።
በማለት ዶሮ አንዴ ሳይጮኽ ሦስቴ ካደው።
ከሦስት ክህደት በዃላ ዶሮ አንዴ ጮኸ፡፡ጴጥሮስም ያኔ ነቃ ፤የጌታው ቃል ትዝ አለው።
ተፀፀተ አለቀሰ አብዝቶ አነባ ፍቅር የሆነው አምላክ ኢየሱስም ፀፀቱን ተቀብሎ እንባውን መዝኖ የበለጠ ሾመው የበለጠ አከበረው የበለጠ ወደደው።
ግን ያ ዶሮ በአንድ ጩኸት ጴጥሮስን ያነቃ ያ ዶሮ ምን አይነት ዶሮ ይሆን? ምንስ አይነት ጩኸት ምንስ ዓይነት ስብከት ነው ያሰማው?
የጴጥሮስስ ልብ እንዴት ያለው ቅን ልብ ነው?የተዘጋጀ ለንሰሃ ቅርብ የሆነ አምላኩን የሚወድ እንደ ይሁዳ ያልጠመመ፣
እንደ ፈርዖንም ያልደነደነ
መልካም እርሻ የሆነ እንዴት የተባረከ ልብ ነው?ዛሬ በየቤተክርስቲያኑ ብዙዎች እንደዶሮው እንጮኻለን፣
ሰሚ የለም፣ምክንያቱም ጩኸታችን የማስመሰል ራስን የመስበክ ዝና ፍለጋ ነውና።
ጩኸታችን የቁራ ጩኸት ነው።
ሰሚየሌለው እንደ ጴጥሮስ ለንሰሃ ሳይሆን የተዘጋና የተቆለፈ ልብ ይዘን ስለሐጢዓታችን ንሰሃ ሳንገባ ስንት ሌሊት ስንት ቀናት አለፉ ።
ዶሮዎቹ ወይም ሰባክያኑ ስለአጯጯኻቸው (ስለስብከታቸው) ቃላት መረጣ እና ፕሮቶኮል ሲጨነቁ፣
ሰሚዎቹም (ምዕመናኑ)በዶሮዎቹ /በሰባክያኑ/ጩኸት ሲደነቁ ብዙ ዘመናት አለፉ፡፡
ጌታሆይ እንደ ጴጥሮስ ቅን ልቦና፣እንደ
ዶሮዉም ለንሰሃ የሚያበቃ አገልጋይ ስጠን።

የሞቱትን ነፍስ በአጸደ ገነት ያሳርፍ።
01/04/2025

የሞቱትን ነፍስ በአጸደ ገነት ያሳርፍ።

Logical and recomended principle for others
01/04/2025

Logical and recomended principle for others

ህይወትን የምትሰጥ እናት ለሆስፒታል ለምን ትከፍላለች? ትራኦሬ‼️

በቡርኪኒፋሶ ከዛሬ ጀምሮ በሁሉም የመንግስት ሆስፒታል ሴቶች ያለምንም ክፍያ በነፃ ልጅ እንዲወልዱ ተወስኗል።

"እኔ የተወለድኩት ከሴት ልጅ ነው ሴት ልጅ ህይወትን ወደ እዚች ምድር ለማምጣት ብዙ ክፍያ ስትጠየቅ ማየት አልፈልግም ።
ድሃ እናቴ እኔን ለመውለድ በሚከፈል ክፍያ ምክንያት እኔን ልታጣ ነበር። ፈጣሪ ባይፈቅድ ኖሮ እኔም በህይወት የለሁም ነበር:: ዛሬ የዚህች አገር ፕሬዚዳንትም አልሆንም ነበር። ስለዚህ ህይወትን የምትሰጥ እናት ለሆስፒታል መክፈል የለባትም።"
የብርኪናፋሶ ፕሬዝደንት ኢብራሂም ትራኦሬ

29/03/2025

# # # # # # ራስ አበበ አረጋይ # # # #
(በፈረስ ስማቸው አባ ገስጥ)

በ፲፰፻፺፮ ዓ.ም በነሀሴ ፲፬ቀን በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት ውስጥ ተወለዱ። የቤተክርስቲያንና ዘመናዊ ትምህርት ተከታትለዋል፤ የክቡር ዘበኛ ሰራዊት አባል ሆነው ሚሊታሪ ሳይንስ በማጥናት በመጀመሪያ የሌተናንት ቀጥሎም የካፕቴንነት ማዕረጎችን ተቀብለዋል። ራስ አበበ አረጋይ በ1928 ዓ. ም ፋሽስት ጣሊያን ኢትዮጵያን ሲወር የአዲስ አባባ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ነበሩ።
በወቅቱ ፋሽስት ኢጣሊያ ከ40 ዓመት በፊት አድዋ ላይ በኢትዮጵያውያን የደረሰባትን አሳፋሪ ሽንፈት ለመበቀል በማይጨው ጦርነት ላይ የተጠቀመቸው በአውሮፕላን የሚረጭ የመርዝ ጋዝ በመሆኑና ከጠላት ጋር አብረው የነበሩት ባንዳዎች ለጣልያን የኢትዮጵያን ምስጢር ይሰጡ ስለነበር በጦርነቱ የወገን ጦር ክፉኛ በመጎዳቱ ንጉሱን ጨምሮ ወደ ኋላ ማፈግፈግ ግድ ሆነ። ከማይጨው ጦርነት በኋላ ጠቅላላ ወታደሩ ወደ ሽምቅ ውጊያ ለመግባት ተገደደ። ራስ አበበ አረጋይ የኢትዮጵያን የነፃነት ሰንደቅ ዓላማ አንግበው አምስት ዓመት ሙሉ በሰሜን ሸዋ (በዱር በገደል)የኢትዮጵያን ሽምቅ ተዋጊዎች በመምራትና የጣሊያን ወራሪ ኃይል አሳፍረው በመመለስ ትልቅ ጀብዱ ፈጽመዋል። ከአምስት ዓመት አርበኝነት ተጋድሎ በኋላ የፋሽስቱ ወራሪ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተጠራርጎ ከኢትዮጵያ ለቋል።

(ከዝክረ ሚያዝያ ፳፯ በፌስቡክ)

23/03/2025

1647 followers, 639 likes, 28 comments

17/03/2025

የመሬት መንቀጥቀጥ

16/03/2025

15.9K likes, 119 comments. “ ”

05/03/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when R50rrmhfiuv posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share