Moges Gashu /Kesis

Moges Gashu /Kesis ሰራዊተ መላእክቲሁ ለመድኃኔዓለም

ክርስትና በጥያቄ ተጀምሮ በመልስ የሚፈጸም ጉዞ ነው ።  ፍትሐዊነትን በሰው ነፍስ ያስቀመጠ እግዚአብሔር ፍትሕን አዘገየ ብሎ ማዘን ተገቢ አይደለም ።  እግዚአብሔር የፍጥረቱን ሁሉ ገደብ የለ...
09/04/2025

ክርስትና በጥያቄ ተጀምሮ በመልስ የሚፈጸም ጉዞ ነው ። ፍትሐዊነትን በሰው ነፍስ ያስቀመጠ እግዚአብሔር ፍትሕን አዘገየ ብሎ ማዘን ተገቢ አይደለም ።

እግዚአብሔር የፍጥረቱን ሁሉ ገደብ የለሽ ጥያቄ ፈርቶ አያውቅም ። እሱ እግዚአብሔር ጥያቄአችንን ስለማይቀየም በፍቅር ይመልስልና ። ሊያውም ለጆሮአችን ሳይሆን ለልባችን ይናገራል ።

በጸሎት በጽናት ለሚሞግተው ሁሉ፣ እግዚአብሔር በርሕረሠሔ ስለሚመልስ በምስጋና አፉን ይሞላል። ችግሮች ተወግደው ሳይሆን ችግሮቹ እያሉ እግዚአብሔር ማስደሰት ይችላል። እግዚአብሔር ችግሩን ትቶ እኛን በመለወጥ ይሠራል ።

ከወጀቡ በፊት የሐዋርያትን የልብ ጥርጣሬ የገሠጸው ከውጭው ማዕበል የውስጡ ማዕበል ስለሚበረታ ነው ። ነገሮች እንዲለወጡ ብቻ ሳይሆን አንተ እንድትለወጥ ለምን።
ማቴ. 8፡26 ።

ታሬ ቃልህን ጠብቀሀልና ቡሩክ ሁን፤ በሰማያውያንና በምድራውያን በረከት ተባረክ።
03/11/2024

ታሬ ቃልህን ጠብቀሀልና ቡሩክ ሁን፤ በሰማያውያንና በምድራውያን በረከት ተባረክ።

ደራሲ መምህር መክት ፋንቱ በእውነቱ ለቤ/ክ ያለህን ቅናት ከሚያውቁ ሰዎች መሀል አንዱ ነኝ ብል ሀሰት የለበትም። ቀርበው ሲያወሩህ ሀሳብ ለመለገስ ጥቂትም ስስት የለብህም። ቅናትህ ይገርመኛል...
12/10/2024

ደራሲ መምህር መክት ፋንቱ በእውነቱ ለቤ/ክ ያለህን ቅናት ከሚያውቁ ሰዎች መሀል አንዱ ነኝ ብል ሀሰት የለበትም። ቀርበው ሲያወሩህ ሀሳብ ለመለገስ ጥቂትም ስስት የለብህም። ቅናትህ ይገርመኛል። ደግሞም ዛሬ በጉራጌ ሀገረ ስብከት ለሚገኘው ለቅዱስ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ከእነ ደራሲ ዶ/ር እንዳለጌታ ከበደ ጋር መጽሐፍት በማሰባሰቡ ረገድ የሰራኸውን ዘላቂ ሥራ ስትነግረኝ አስደምመኸኛል። ይኽንኑ ለብፁዕነታቸው ነግሬ ግርም ብሎአቸዋል። ገና ብዙ እንጠብቃለንና በርታልኝ የልቤ ሰው። ብዙ ማድረግ ትችላለኽ። ይኼንን መንፈሳዊ ኮሌጃችንን እንዴት እናግዝ የሚለው ሀሳብ የሁላችንም የጋራ አጀንዳ ይሆን ዘንድ ደራሲ መክት ፋንቱን እንድታዋዩት አድራሻ ተውኩላችሁ። +251911879692
ደግሞም የኮሌጁን ዲን የክቡር መጋቤ ስብሐት ሳህሉን ስልክ እነሆ። 0911598912

"አገልግሎት ከፊት ሹመት ፣ ከኋላ ሽልማት አለው ። አገልግሎት ሹመት ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነት አለው ።  አገልግሎት ዕድል ብቻ ሳይሆን አደራም ነው።እግዚአብሔር የምንደሰትበት ብቻ ሳይሆን የሚ...
03/10/2024

"አገልግሎት ከፊት ሹመት ፣ ከኋላ ሽልማት አለው ። አገልግሎት ሹመት ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነት አለው ። አገልግሎት ዕድል ብቻ ሳይሆን አደራም ነው።እግዚአብሔር የምንደሰትበት ብቻ ሳይሆን የሚደሰትብን መሆኑን በማሰብ በትጋት ማገልገል ይገባል።"

27/09/2024

"የክርስቶስ መስቀል እግዚአብሔር ፍቅሩን ለዓለም የሰበከበት አትሮንስ ነው፡፡"

ቅዱስ አውግስጢኖስ

የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና።1ኛ ቆሮ 1፥18
26/09/2024

የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኀይል ነውና።
1ኛ ቆሮ 1፥18

ከሁሉ የሚበልጠው አባትነት መንፈሳዊ አባትነት ነው ። ምድራውያን አባቶች ይህን ዓለም ለማየት ምክንያት ሲሆኑን መንፈሳውያን አባቶች ደግሞ ሰማያዊውን ዓለም ለማየት ያበቁናል ። ምድራውያን አባ...
25/09/2024

ከሁሉ የሚበልጠው አባትነት መንፈሳዊ አባትነት ነው ። ምድራውያን አባቶች ይህን ዓለም ለማየት ምክንያት ሲሆኑን መንፈሳውያን አባቶች ደግሞ ሰማያዊውን ዓለም ለማየት ያበቁናል ። ምድራውያን አባቶች የወለዱት ሥጋችንንም ነፍሳችንንም ሳለ የሚያስቡት ግን በአብዛኛው ለሥጋችን ነው ። መንፈሳውያን አባቶች ግን ነፍሳችንን ለማዳን ይተጋሉ ። ምድራዊ አባትነት ሞት ይሽረዋል ። መንፈሳዊ አባቶች ግን ዝምድናቸው ዘላለማዊ ነው ። ለመንፈሳዊ አባቶቻችን በሁኔታ የማይለወጥ ውዴታና አክብሮት ልንሰጥ ይገባል። መንፈሳውያን አባቶቻችን የነፍስ ሀኪሞቻችን ናቸውና።

23/09/2024

" 'መዳን በሌላ በማንም የለም' የሚለው ቃል እግዚአብሔርን ላከበሩ፤ እርሱም ላከበራቸውና ለሚጸልዩልን ቅዱሳን መቃወሚያ ተደርጎ የሚጠቀስ ሳይሆን ክርስቶስን ገድለው ስሙ ሲነሣ ለሚከፉ ሰቃልያነ እግዚእ የተጠቀሰ ነው ። እነዚህ ወገኖች ሌላ አዳኝ የለምና የሰቀሉትን ጌታና አዳኝ ብለው ማመን ነበረባቸውና ነው።"

21/09/2024

"አድርግ አታድርግ የሚለውን ሕግ ጨዋ ያሳደጋቸው ልጆች ይጠብቃሉ። አይገድሉም፣ አይሰርቁም፣ አይሳደቡም። በእውነት ክርስትና ግን ከዚህ ጨዋነት በላይ ነው። ክርስቲያን የሆነው ፖሊስን ላለማስቸገር ብቻ አይደለም። የዓለምን ሕመም ለመቀነስም ነው። የዓለምን ሕመም የምንቀንሰው የሚያለቅሱትን እንባቸውን በማበስ፣ ያዘኑት በማጽናናት፣ የወደቁትን በማንሣት ነው። በክርስትናችን ልዩነት ፈጣሪ መሆን ይገባናል እንጂ ተመሳስሎ ኗሪ መሆን አይገባን። አንተ ባለማኅተሙ በመኖርህ የሆነ የሚተው ክፉ ሥራ መኖር አለበት። "

" ነገር ግን፥ ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሠኘችው።ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።እርሷም በ...
12/09/2024

" ነገር ግን፥ ሄሮድስ የተወለደበት ቀን በሆነ ጊዜ፥ የሄሮድያዳ ልጅ በመካከላቸው ዘፈነች ሄሮድስንም ደስ አሠኘችው።
ስለዚህም የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት በመሐላ ተስፋ አደረገላት።
እርሷም በእናቷ ተመክራ፦ የመጥምቁን የዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት ስጠኝ አለችው።
ንጉሡም ዐዘነ፥ ነገር ግን፥ ስለ መሐላው ከርሱም ጋራ ተቀምጠው ስላሉት ሰዎች እንዲሰጧት አዘዘ።
ልኮም የዮሐንስን ራስ በወህኒ አስቈረጠው። ራሱንም በወጭት አምጥተው ለብላቴናዪቱ ሰጧት፥ ወደ እናቷም ወሰደችው።"
ማቴ 14፥6-11

በአዲሱ ዓመት🌼 እግዚአብሔር ቤታችሁን በደስታ፣ ልባችሁን በፍቅር💛 ህይወታችሁን በስኬት፣  ይሙላው🌼 ክፉ ይራቅላችሁ ደግ ደጉ ይቅረባችሁ🌼
10/09/2024

በአዲሱ ዓመት🌼 እግዚአብሔር ቤታችሁን በደስታ፣ ልባችሁን በፍቅር💛 ህይወታችሁን በስኬት፣ ይሙላው🌼 ክፉ ይራቅላችሁ ደግ ደጉ ይቅረባችሁ🌼

Address

Welkite
Wolkite

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251961256883

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Moges Gashu /Kesis posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share