27/10/2025
"የህግ ማስከበር ስራችንን አጠናክረን እንቀጥላለን"
የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር
የሰሜን ሸዋ ዞን ጠቅላላ አመራር የባለፋት ወራት የሰላምና ልማት ስራዎችን ገምግሟል ።
በግምገማውም በቀጠናው እየተከናወነ ያለውን ዝርዝር የህግ ማስከበር እና የልማት ስራ አፈፃፀም ቀርበው ተገምግመዋል ።
በየወረዳው እና ከተማ አስተዳደሮች የተከናወኑ የሰላምና ልማት ስራዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻል እንዳሳዩም ተመላክቷል።
ቀበሌን ማዕከል ያደረገ ህዝባዊ ውይይቶች ፣ ወረዳና ቀበሌ ራስን ማስቻል ፣ ህዝቡን የሰላሙ ባለቤት እንዲሆን ማድረግ ላይ የተሰራው ስራ አበረታች ውጤት እንደተገኘባቸው ተገልጿል ።
በቀጣይም ይኸው ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ።
ከልማት ስራ ጋር በተያያዘ የመስኖ ፣ ተፈጥሮ ሃብት ቅድመ ዝግጅት ፣ ትምህርት፣ ጤና ፣ ገቢ አሰባሰብና ስራ እድል ፈጠራ ተግባራት በጥልቀት ተገምግሟል ።
በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ ራሱ ለለውጥ ተነሳስቶ መላ ህዝቡን በማነሳሳት የታቀዱ ግቦች ሁሉ እንዲሳኩ ርብርብ እንደሚደረግ መግባባት ላይ ተደርሷል።