04/12/2025
በጎንደር የሰላም ጥሪ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው
*********************************
(ሕዳር 25/2018 ቦንጋ አጥናፍ ፕሮሞሽንና ኢቨንት) የጎንደር ከተማ እና የማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በጋራ ያዘጋጁት የሰላም ጥሪ የድጋፍ ሰልፍ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ ነው።
በጎንደር ከተማ እየተካሄደ ባለው የሰላም ጥሪ ሰልፍ ላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።
በሰልፉ ላይ ሰላምን ለማጽናትና አብሮነትን ለማጠናከር የሚያስችሉ መልዕክቶች ተላልፈዋል።
በዚህም የሃይማኖት ተቋማት የሚያደርጉት ውይይት ግጭትን ለመፍታት ወሳኝ መሳሪያ ነው! ቤተእምነቶች ሰላም ማስፈን ተቀዳሚ ተግባራቸው ነው! ሰላም፣ አንድነትና አብሮነት ከሃይማኖት ተቋም የተቀዱ ናቸው! የሚሉ መፈክሮች ተሰምተዋል።
በተጨማሪም ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን የአብሮነታችንና የጥንካሬዎቻችን መሰረቶች ናቸው! ሃይማኖት የሰላም መሰረት ነው! የሰላምና የመከባበር ባህልን ለማስቀጠል የሃይማኖት ተቋማት ሚና የማይተካ ነው! በሚል መልዕክት በማስተላለፍ ህብረተሰቡ ለሰላምና አብሮነት ያለውን ፍላጎት አንጸባርቋል።
ዘገባው የአሚኮ ነው