Ashebir Zaza

Ashebir Zaza Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ashebir Zaza, Event Planner, Main road, Arba Minch'.

09/04/2026

ይህንን ሁሉ ካርድ ምርጫ አስፈፃሚዎች አናስጥልም ካሉ ምን እንሆናለን ሲሉ ዛሬ መስማቴን እንድታዉቁ እፈልጋለሁ።

ደመወዝ የላብ ውጤት በመሆኑ፣ ሰራተኛው ለሚያበረክተው ጉልበት፣ ጊዜና እውቀት የሚከፈለው ተመጣጣኝ ክፍያ ነው። በችሮታ የሚያገኘው አይደለም። ደመወዝ የሰራተኛው የላብ እና የጥረቱ ፍሬ ነው። ...
07/04/2026

ደመወዝ የላብ ውጤት በመሆኑ፣ ሰራተኛው ለሚያበረክተው ጉልበት፣ ጊዜና እውቀት የሚከፈለው ተመጣጣኝ ክፍያ ነው። በችሮታ የሚያገኘው አይደለም።
ደመወዝ የሰራተኛው የላብ እና የጥረቱ ፍሬ ነው። የሰራተኛ ደመወዝ መከልከል አረመኔያዊነት ነው።

ምንድነው ጉዱ?ከባነር ሽቀላ እንጂ አማረኛ ግድ የሌላቸው ማተሚያ ቤቶችና ኮሚሽን የሚቀበሉ ትዕዛዝ ሰጪዎች የማያሳዩን ጉድ የለምኮ ፈደል ይገላል ሲሉ 'ጽ' ገደለቻቸዉ እግዝኦ ማሪነ ክርስቶስ!
30/03/2026

ምንድነው ጉዱ?
ከባነር ሽቀላ እንጂ አማረኛ ግድ የሌላቸው ማተሚያ ቤቶችና ኮሚሽን የሚቀበሉ ትዕዛዝ ሰጪዎች የማያሳዩን ጉድ የለምኮ ፈደል ይገላል ሲሉ 'ጽ' ገደለቻቸዉ እግዝኦ ማሪነ ክርስቶስ!

29/03/2026

እጅግ ብዙ የሚዘገንኑ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ በተቋማችን ምነው ለምርጫ ሥራ የመንግሥትና ህዝብ በጀት እንደፈለጉ መጫወት ይፈቀድልን? በየቀኑ ስንት ገሱባ ዉስጥ...

25/03/2026

በኔትወርክ ለቀሩት ሪፎርሙ ወላይታ ዉስጥ ሁሉም ቦታ ይዳረስ፣በተለይ ገሱባ አለበለዚያ አስገድዶ ካርድ ያስወሰዱ በአፈና ድምፅ ሊያሰጡን አይችሉም።

23/03/2026

: No Health No Election ‼️
Comment bollan suntta mention oottitte!👏
#የተዘጋውን ሆስፕታል በሙሉ አቅም ክፈቱ!
ሰው ታሞ ህክምና ከዓመት በኋላ እንሰጣለን አይባልም! በሽታ ጊዜ አይሰጥም ይገድላል! የሚሊዮኖች መታከሚያ ሆስፕታል ወድሞ ዓመት በላይ ህዝቡ እንዳይታከም ሞት እንዲጨምር እናቶች እንዲሰቃዩ ህፃናት ተስፋ እንዲያጡ ማድረግ ወንጀል ነው! ኦቶና ሆስፕታል ወደነበረበት መልሱ!


Ministry of Health,Ethiopia
Dr Mekdes Daba, Minister of Health
Abiy Ahmed Ali
World Health Organization (WHO)
Tedros Adhanom Ghebreyesus
Frehiwot Abebe
Wolaita S**o University

ወ/ሮ አብጋል አበራ ቦታው ቀጥር 06745 ኮድ M-102  ብሩህተስፋ ቀበሌ ሆስፒታል መንደር 300,000 ብር በ08/09/2018 ሽጣለች።የአዜሄል መሬት እንደሆነ ብታወቅም የግለሰቧ እንደሆነ...
21/03/2026

ወ/ሮ አብጋል አበራ ቦታው ቀጥር 06745 ኮድ M-102 ብሩህተስፋ ቀበሌ ሆስፒታል መንደር 300,000 ብር በ08/09/2018 ሽጣለች።የአዜሄል መሬት እንደሆነ ብታወቅም የግለሰቧ እንደሆነ ማስተባበያ ኢዮብ አበራ ቢሰጥም ቦታ ቁጥር 06746 ኮድ -3 በክሩበል ገብሬ ስም ያለው የማን ይሁን? ወይዘሮዋ በሴቶችና ህፃናት በተላላኪነት 1300 ብር ተቀጥራ እየሰራች የጨረቃ መሬት የመግዛት አቅም አላት ብለዉ ነዉ አስተባባሪ አካላት ማዘጋጃ ላይ አሻራ ለማስቀመጥ ከመስክ ወጥታ እንድትሄድ ሐሙስ የፈቀዱላት የሚለው ሌላ ጥያቄ የፈጠረብን ሆኗል። አስተባባሪው ከፋይናንስ እና ማዘጋጃ መሬት እጁን ካላነሳ መፃፋችን ይቀጥላል። የፋይናንስ ዝርፊያ በተግባር እየተረጋገጠ ዳግም ወደ ክፊያ ኬዝ ቲም እንመልሳለን ብለዉ ከንቱ ልፋት ነዉ ያልተወዳደቁ ሰነዶች ከ6 ሚሊየን በላይ መሆናቸውን ደጋግመን ለመፃፍ እንገደዳለን።

ማሰር መሸነፍ ነዉ፣ስንት ሚሊዮን ብር በግለሰቦች ተበዝብዘዋል በሰነድ ተቀብለው ባለዕዳ ሆነዉ የመንግሥት ዉስን ሀብት ለግል ብልጽግና ማዋላቸውን ጥቆማ ስለሰጠና በሚዲያ ስላጋለጠ 21 ቀን ጊዜ...
17/03/2026

ማሰር መሸነፍ ነዉ፣ስንት ሚሊዮን ብር በግለሰቦች ተበዝብዘዋል በሰነድ ተቀብለው ባለዕዳ ሆነዉ የመንግሥት ዉስን ሀብት ለግል ብልጽግና ማዋላቸውን ጥቆማ ስለሰጠና በሚዲያ ስላጋለጠ 21 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ዋስትና ተከልክለው ታስሮ የወጣ የገለባ ከተማ አስተዳደር ባለሙያ ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል። ተረኞች የእናንተ አይርቅም ሌቦችን በሙሉ ሊያስገባችሁ ተቃርቧልና።
እንኳንስ ለቤትህ አበቃ እዉነት መቼም ተደብቃ አትቀርም በርታ።

ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመለሱ+++++++++++++++++++++++  | ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ መደ...
11/03/2026

ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመለሱ
+++++++++++++++++++++++

| ከህግ ውጪ ከሥራቸው የተሰናበቱ 942 ሰራተኞች ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም አስታወቀ፡፡

“የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት እመርታ፤ ለተሳካ ሀገረ መንግስት ግንባታ” በሚል መሪ ሀሳብ ሀገራዊ የዳኝነትና የዲሞክራሲ ተቋማት የሪፎርም ጉዞን የሚዳስስና ቀጣይ አቅጣጫዎችን የሚመለከት ኮንፈረስ ተካሂዷል፡፡

የተቋሙ ዋና ዕንባ ጠባቂ ወይዘሮ ስመኝ ውቤ በኮንፈረንሱ ላይ እንደገለጹት፤ የህዝብ አስተዳደር እንዲሻሻልና የመንግስት ተጠያቂነት ለማሳደግ ይሰራል፡፡

አስተዳደራዊ በደል የደረሰባቸው ግለሰቦች የሚያቀርቧቸውን ቅተሬታዎችና አቤቱታዎች በመከታተል መምርምሮ እልባት እንዲያገኙ እየሰራ ይገኛል፡፡ በቀጣይም የአቤቱታ ምላሽ አሰጣጡን ከ78 በመቶ ወደ 85 በመቶ ለማድረስ መታቀዱን ገልጸዋል፡፡

ባለፉት ዓመታት በተሰሩ ሥራዎች ወደ ተቋሙ ከሚመጡ አቤቱታዎች መካከል 78 በመቶው እልባት እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ ለአስተዳደራዊ በደል ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የቁጥጥር ሥራዎችን በመስራት 87 በመቶ መፍትሔ እንዲያኙ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡

እንደዋና ዕንባ ጠባቂዋ ገለጻ፤ መሬታቸው ያለአግባብ የተወሰደባቸው 828 አቤቱታ አቅራቢዎች ጉዳያቸው ተመርምሮ ምትክ ቦታ እንዲሰጣቸውና 14 ሚሊየን ብር ካሳ እንዲከፈላቸው ተደርጓል፡፡ ከህግ ውጪ ከሥራቸው ተሰናብተው የነበሩ 942 ሰራተኞች ደግሞ ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ መደረጉን አብራርተዋል፡፡

አቤቱታ አቅራቢዎች ከህግ አግባብ ውጪ የተከለከሉትን ልዩ ልዩ መንግሥታዊ አገልግሎቶች እንዲያገኙ መደረጉን ጠቅሰው፤ ዜጎች መረጃ የማግኘት፤ የመጠየቅ፣ የማዘጋጀት መብታቸው እንዲከበርና የመረጃ ነጻነት ህጉ እንዲተገበር ክትትል እያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡፡

የተጠናከረ የቁጥጥርና የምርመራ ሥርዓትን መዘርጋት፤ የአስተዳደራዊ በደል እንዲቀንስ መስራት የተቋሙ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የህዝብ አስተዳደር በግልጽነትና በተጠያቂነት መርህ እንዲመራ ለማድረግና ህገ መንግሥታዊነትን ለማስፈን እንደሚሰራ በመግለጽ፤ ተቋማት የሚሰጧቸው ፍትሃዊነት የጎደለው ውሳኔዎችና ትዕዛዞች በወቅቱ ለማረምና ለመከላከል እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በማርቆስ በላይ
+++++++++++++++++++++++++
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ #መረጃ ነጻነት

11/03/2026

ከ40 በላይ ህገወጥ ቅጥር ሳይታረም ደመወዝ እየበሉ ባሉበት ከተማ ከሹመት የተነሱ የመንግሥት አመራሮችን ደመወዝ እንድያዝ ማድረጉም ሆነ ከፋይናንስ ዩኒቲ ለመሆን መሯሯጥ ተገቢነት የለዉም።

11/03/2026

ታጋዮችን በማሰር በዉስጥና በዉጪ የሚሰሩ የፋይናንስ ህግ ጥሰቶች እንዳይወጡ ማድረግ አይቻልም።ከ6 ዓመት በላይ ያለመደብ ደመወዝ የሚበሉትን ዝም ብሎ ዩኒቲዎች ላይ ማትኮር ለምን አስፈለገ?

Address

Main Road
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ashebir Zaza posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category