Saro Media Network

Saro Media Network ወቅታዊ ፣ ታማኝ እና ሚዛናዊ መረጃ የሚያገኙበት ገጽ ነው ‼️

ፍቅር ህዝብ ❤
23/07/2025

ፍቅር ህዝብ ❤

ከተረጅነት ለመላቀቅና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንሴት ከፍተኛ ሚና አለው 🔔  🇪🇹
23/07/2025

ከተረጅነት ለመላቀቅና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንሴት ከፍተኛ ሚና አለው 🔔

🇪🇹

የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር አቶ መለሰ ማርካን የመጀመሪያው ዋና ከንቲባ አድርጎ ሰየመበጋሞ ዞን የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤት ምስረታ አስቸኳይ ጉባኤውን በማድረግ የስራ አ...
23/07/2025

የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር አቶ መለሰ ማርካን የመጀመሪያው ዋና ከንቲባ አድርጎ ሰየመ

በጋሞ ዞን የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ጊዜያዊ አማካሪ ምክር ቤት ምስረታ አስቸኳይ ጉባኤውን በማድረግ የስራ አስፈጻሚ ሹመቶችን አፀደቀ

‎የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ጊዚያዊ አማካሪ ምክር ቤት ምስረታ ጉባኤውን በማድረግ ለምክር ቤት አባላት የቀረቡ እጩዎች ላይ ሀሳብ በመስጠት በሙሉ ድምፅ አስፈጻሚ ሹመቶችን አጽድቋል።

‎በዚህም መሰረት፤
‎1/ አቶ መለሰ ማርካ- የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ዋና ከንቲባ -
‎2/ አቶ አምሳሉ ሶባ - የዘፍኔ ከተማ አስተዳደር ጊዚያዊ አማካሪ ምክር ቤት-ዋና አፈ - ጉባኤ
‎3/ አቶ አለሙ ወ/ጊዮርጊስ - የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፍ /ጽ/ቤት ኃላፊ
‎4/ አቶ መስፍን ሙሉ - የከተማው ም/ከንቲባና የስራ ዕድል ፈጠራና እንተርፕራይዝ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ
‎5/ ኢ/ር ብርሃኑ ኩሉሉ - የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፍ ጽ/ቤት ፓለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ
‎6/ አቶ ህዝቅኤል መለሰ የከተማው ብልጽግና ፓርቲ ቅ/ፍ ጽ/ቤት አደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ተሹመዋል።


እናት የፍቅር ጥግ ❤
23/07/2025

እናት የፍቅር ጥግ ❤

23/07/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Dawit Bonga, Ashebir Zlk, Muhammad Hussein Sheraga, Dagnachew Daniel, Shani Ye Eyob, Tamiru Chonka, Yacob Segno Miracle, Feleke Firew, Ketema Beyene, Amanuel Ayza Anebo, Abedurzak Zemedkun, Teshale Tefera, Zenebe Bute, Tariku Mathewos, Wondiye Geta, Desu Kuma, Daniel Tadesse, Samuel Tadese, Wuro Wondu, Muluken Desalegn Dore, Taye Ye Covenant Lij, Getako Yichilal, Ende Fekadu Yehun, Munea Tesfaye, Habtamu Yadessa Gemeda, Aschallew Getachew, Chernet Bafa, ጊዜው የሁላችን ነው, Habtamu Shano Kassa, Feleke Haile, ሃብታሙ መስፍን ተሰማ, Desalegn Damako Darato, Getasew Bogale Abrie, Yonas Kacho, Abdulkerim Hussien, NbTamirat GDode Nado, Zerihun Shiferaw, Abdi Hassen, Fkre Dawt Mami, Gunner's Chukayo, Habtamu Abe, Belete Argaw, Duke Mamude, Getahun Markos Aneshu, Eliyas Hameraw, Kenbon Dejene, Biniyam Teshome, Zelalem Tigabu, Bazezew Tariku, Sint Ayehu Tesfaye

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ከዞኑ ሳይንስ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ መምሪያ ጋር በመተባበር  የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና በክረምት ወራት ከወጣቶች በጎ ፍቃድ ሥራ ጋ...
22/07/2025

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ከዞኑ ሳይንስ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጅ መምሪያ ጋር በመተባበር የኢትዮ-ኮደርስ ሥልጠና በክረምት ወራት ከወጣቶች በጎ ፍቃድ ሥራ ጋር ሥልጠናውን በኦፋ ወረዳ አስጀምሯል።

የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ወጣት ታደለ ሜጋ በኦፋ ወረዳ ባስጀመሩበት ወቅት በክረምት ወራት ከወጣቶች በጎ ፍቃድ ሥራ ጋር 5 ሚሊየን ኮደርስ ስልጠና የዲጂታል ክህሎትን በማሳደግ ሥልጠናው እንደሀገር ተጠናክሮ መቀጠሉን አብራርተዋል

የ''አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ ስልጠና የዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት፣ እውቀትን መሰረት ያደረገና ምክንያታዊ ውሳኔዎችን መስጠት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ማግኘት የሚቻልበት እንደሆነ ወጣቶች ገለጹ፣

ኃላፊው የ''አምስት ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ’’ ስልጠና ሐምሌ 2016 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይፋ መደረጉ ይታወሳል ብለዋል።

ስልጠናውን የተከታተሉ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ክህሎት ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸውና ለስራቸው ተጨማሪ ክህሎትና እውቀት ያስጨበጣቸው መሆኑን ገልፀዋል።

አቶ ምህረቱ ዳና የወላይታ ዞን የወጣቶች ምክር ቤት ፕረዚዳንት እንዳብራሩት የዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ከመሰረተ ልማትና አስቻይ ስርዓት ከመዘርጋት በተጨማሪ የዲጂታል ክህሎት ያለው ማህበረሰብ አስፈላጊ እንደሆነና የሚሰጠው ስልጠና ከዲጂታል ክህሎት በተጨማሪ እውቀትን መሰረት ያደረገና ምክንያታዊ ውሳኔዎችን መስጠት የሚያስችሉ ክህሎቶችን ማግኘት የሚቻልበት እንደሆነም በማወቅ ሁሉም ወጣቶች የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪም ቀርቧል።

በተያያዘ ዜና የወላይታ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ወጣቶች ክንፍ የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ አጠናክሮ መቀጠሉን የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ጠቁመዋል ።

“የዲጅታል ኢትዮጵያ” ግቦች በማሳካት ሂደት ፋይዳ ብሄራዊ መታወቂያ ትልቅ ድርሻ አለው።

ፋይዳ የብሄራዊ መታወቂያ አሰጣጥን ማሳካት በርካታ ጥቅሞች ያሉት መሆኑንና፣ ከእነዚህም መካከል፤ የዲጅታል ሲስተም ተጠቃሚ ህዝብ በመፍጠር፤ ኢኮኖሚው በዲጅታል እንዲከናወን፣ የመንግስት አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ ያለመ መሆኑን የወጣቶች ክንፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አብራርተዋል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መልካም አስተዳደርን ለማረጋገጥ፣ የተጀመረውን ሪፎርም ሥራ የተሟላ በማድረግ፣ የተለያዩ ህገወጥ ተግባራትን መቆጣጠር፣ አስተማማኝ ሰላም ለማስፈን፣ የንግድ ስርአቱን እና የገቢ አሰባሰብ ስርዓት ለማዘመን ቁልፍ ሚና ይጫወታል ብለዋል።

በዞኑ በክረምት ወራት ከወጣቶች በጎ ፍቃድ ሥራ ጋር የኮደርስ ስልጠናና ፋይዳ የብሄራዊ መታወቂያ ምዝገባ በተጨማሪም ተከታታይነት ያለውና ለወጣቶች ወሳኝ ጉዳይ መሆኑን ተገልጿል።

የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ አመራሮች አዳዲስ ሹመቶችና ሽግሽግ አደረገ።አርባ ምንጭ ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም (የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን)፦@ #በዚህ...
22/07/2025

የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር የተለያዩ አመራሮች አዳዲስ ሹመቶችና ሽግሽግ አደረገ።

አርባ ምንጭ ሐምሌ 15/2017 ዓ.ም (የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን)፦

@ #በዚህ መሠረት በካቢኔ ማዕረግ ሽግሽግ፦

1. አቶ አበበ ፔዣ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ እና ትራንስፖርት መንገድ ልማት ጽ/ቤት ኃላፍ፣
2.አቶ ጌታሁን ሼጋ ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ፣
3.ምትኩ ኤልያስ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ፣
4. አቶ ማትዮስ መለሰ ፐብሊክ ሰርቪስ የሰው ሀብ ልማት ጽ/ቤት
5. ሀብታሙ በየኔ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ፣
6. አቶ ብልሃቱ ቢሆነኝ መልካም አስተዳደርና አከባቢ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፍ

@ #በምክትል ማዕረግ
1.አቶ ወንድሙ ጨሌ ህብረት ሥራ ልማት ጽ/ቤት ኃላፊ፣
2. አቶ እንዳልካቸው ኢሳያይስ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊ፣
3.አቶ እንድሪያስ ጫሜ የብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ኃላፊ
4. ወ/ሮ ህይወት ጮራ ፋይናንስ ጽ/ቤት የጋራ አገልግሎት ፑል ኃላፊ፣
5.አቶ ፊልሞን ዳባ ሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ፣

@ #አዲስ ሹመት በምክትል ማዕረግ
1. ሀና ኤልያስ ፋይናንስ ጽ/ቤት ሲቭክ ትብብርና በጀት ዘርፍ ኃላፊ፣
2. ስንታየሁ ሳማየ ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ፣
3. አቶ ታጋሽ ግርማ ግብርና ጽ/ቤት እንስሳት ዓሣ ሀብት ልማት ዘርፍ ኃላፊ፣

@ #ታዳጊ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት፦
1. አቶ ምንተስኖት ዘርይሁን ዜይሴ ኤልጎ ታዳጊ ማዘጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ
2. እስማኤል ጉባኤ የዜይሴ ወዜቃ ማዜጋጃ ቤታዊ አገልግሎት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተሹመዋል።

የመንገዱ መጀመር ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ጥያቄን የሚያዳምጥና የሚመልስ ለመሆኑ ማሳያ ነው- አቶ ኃ/ማርያም ተስፋዬበጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ከዛዝኤ ካምኣሌ በርኤ  ኦሮ እስከ ዛላ ዶላ ቀ...
22/07/2025

የመንገዱ መጀመር ብልፅግና ፓርቲ የህዝብ ጥያቄን የሚያዳምጥና የሚመልስ ለመሆኑ ማሳያ ነው- አቶ ኃ/ማርያም ተስፋዬ

በጋሞ ዞን ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ከዛዝኤ ካምኣሌ በርኤ ኦሮ እስከ ዛላ ዶላ ቀበሌ በአለም ባንክ ድጋፍ ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኘው የ13.3 ኪ/ሜ የገጠር ትስስር መንገድ ስራ በይፋ ተጀምሯል።‌‎

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ኃ/ማርያም ተስፋዬ የመንገድ ተደራሽነትን ማስፋት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዋል።‌‎

የመንገድ ስራው ከ13 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያለው መሆኑን የገለፁት አቶ ሃይለማርያም ከ64 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጭ እንሚደረግበትና በ6 ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ አብራርተዋል።‌‎

በገረሴ ዛሬ የተጀመረው ቀበሌን ከቀበሌ የሚያገናኘው የገጠር መንገድ የብልጽግና መንግሥት ህዝብን የሚሰማና ጥያቄያቸውን በተገቢው መልኩ የሚመልስ ፓርቲ መሆኑን ማሳያ እንደሆነ ገልፀዋል።‌‎

መንገዱ ሲጠናቅ ለአርሶ አደሩ ቴክኖሎጅ በማድረስና ያመረተውን ምርት ለገበያ እንዲያቀርብ እድል እንደሚፈጥርለት ጠቁመዋል።‌‎

የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ በማስጀመሪያው መርሃ - ግብር ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ሰባት አመታት መንግስት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ለውጥ በማምጣት ህዝቡን ተጠቃሚ ማድረጉን አስረድተዋል።‌‎

ወረዳው በርካታ ፀጋዎች የሚገኙበት አከባቢ በመሆኑ ‎ያሉ ፀጋዎችን በአግባቡ በመጠቀም የህዝቡን የመልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን መፍታት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል።‌‎

የዞኑ መንግስት ለመንገድ ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የህዝቡን የዘመናት ጥያቄዎችን ሲመልስ መቆየቱን ዶ/ር ደምሴ አስታውሰው በዛሬው ዕለት 4 ቀበሌዎችን የሚያገናኝ መንገድ በተባለለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ህብረተሰቡ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ አሳስበዋል።‌‎

የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ቦርሴ ቦታ እንደተናገሩት የመንገዱ የህዝቡ የዘመናት ጥያቄ መሆኑን ተናግረው የመንገድ ስራው በመጀመሩ መደሰታቸውን በመግልፅ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የመንገድ ልማት በወረዳው የተጀመሩ ልማቶችን ለማሳካት ወሳኝ በሆኑ በትኩረት እንደሚሰራም ገልፀዋል።‌‎

መንገዱ የክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ከአለም ባንክ ጋር በጋራ የሚያሰሩ መሆኑም ተመላክቷል።‌‎

በማስጀመሪያ መድረኩ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልሉ ትራንስፖርትና መንገድ ልማት ቢሮ አቶ ሃይለማርያም ተስፋዬ ፣ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳደሪ ዶ/ር ደምሴ አድማሱ ፣ የጋሞ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ ሀኪሜ አየለን ጨምሮ የክልል ፣ የዞንና የወረዳው አመራሮች ፣ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።‎

22/07/2025




ሰበር የፍርድ ቤት ውሳኔ ዜና* 16 ዓመት አደይ ጌታቸው ፅኑ እስራት * 15 ዓመት ሉንጎ ሉቃስ ፅኑ እስራት የአለልኝ አዘነ ግድያ እና የተላለፈው ፍርድ!የቀድሞው እግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ ...
22/07/2025

ሰበር የፍርድ ቤት ውሳኔ ዜና

* 16 ዓመት አደይ ጌታቸው ፅኑ እስራት
* 15 ዓመት ሉንጎ ሉቃስ ፅኑ እስራት

የአለልኝ አዘነ ግድያ እና የተላለፈው ፍርድ!

የቀድሞው እግር ኳስ ተጫዋች አለልኝ አዘነን በመግደል ወንጀል ተከሰው የነበሩት ባለቤቱ ወ/ሮ አደይ ጌታቸው እና የእህቷ ባል ሉንጎ ሉቃስ በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጽኑ እስራት ተፈረደባቸው።

ፍርድ ቤቱ በዛሬው ዕለት ባስተላለፈው ውሳኔ፣

1. ወ/ሮ አደይ ጌታቸው የ16 ዓመት ጽኑ እስራት ሲፈረድባቸው፣

2. የባለቤቱ የእህቷ ባል (ሉንጎ ሉቃስ) ላይ ደግሞ የ15 ዓመት ጽኑ እስራት ተበይኖበታል።

ይህ አስደንጋጭ ክስተት የተከሰተው አለልኝ አዘነ እና ባለቤቱ ከተጋቡ ከ15 ቀናት በኋላ መጋቢት 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ነበር።

ፍርድ ቤቱ በሰውና በሰነድ ማስረጃዎች መሠረት ወንጀሉ መፈጸሙን ካረጋገጠ በኋላ ይህን ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል።

የአለልኝ አዘነ ግድያ በብዙዎች ዘንድ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ክስተት ሆኖ ሲነገር ቆይቷል።

ፍርዱን እንዴት አያችሁት

ሀሳባችሁን አካፍሉ

ጀግናን ጀግና አለማለት ... ንፉግነት ነው ።የለውጡ መሀንዲስ ፣ አርቆ አሳቢ ጥበበኛ መሪ ፣ በ2 ዓመት እድሜ  ክልሉን በአገራችን ከሚገኙ  ነባር ክልሎች በለውጥ ጉዞው  እጅን በአፍ የሚያ...
22/07/2025

ጀግናን ጀግና አለማለት ... ንፉግነት ነው ።

የለውጡ መሀንዲስ ፣ አርቆ አሳቢ ጥበበኛ መሪ ፣ በ2 ዓመት እድሜ ክልሉን በአገራችን ከሚገኙ ነባር ክልሎች በለውጥ ጉዞው እጅን በአፍ የሚያስጭን ውጤት በማስመዝገብ ግንባር ቀደም ያደረገ ቅንና አስተዋይ የህዝብ ልጅ , ክብር ይገባዋል 🙏🙏 Respect !

ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል በመስራቱ የህዝቡን ሁለንተናዊ የልማት ፍላጎትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት በተደረገው ጥረት ከፍተኛ የሆነ በአይን የሚታዩ ፣ የሚቆጠሩ በርካታ ውጤቶች አምጥቷል ።

እግሮች ሁሉ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ እንዲጎርፉ በምድር ብቻ ሳይሆን አየር መንገዱን አጨናንቆ እንዲመጣ የሆነበት ፣ የአገር መሪን ልብ ሳይቀር ቀልብ እንዲሳብ የተደረገበት፣ አለምን ያስደመመ ውጤት የመጣው በስራ ነው።

እና ...ጀግናን ጀግና አለማለት ... ንፉግነት አይሆንብንም

የለውጡ መሀንዲስ ባሳየሄን መንገድ አብረን እንስራ ብሎ ከመደገፍ ስራን ማጣጣል አይን ያወጣ በሬ ወለደ ውሸት መቀባጠር የሰውኛ ሳይሆን ሰይጣናዊ አስተሳሰብ ነው ።

ለዚህ ነው የፅንፈኞች ራስ ምታት የሆነ መሪ አለን የምንለው , ሰርቶ የሚያሰራ ጀግናን ;ምቀኛ ከህዝብ የራቀ ጭፍን ጥላቻን የሚያንፀባርቅ ሴረኛ ለደቂቃ ከለውጥ ጎዳና አያስቆምም።

ለዘመናት አይተንም ሰምተንም የማናውቀውን እውነተኛ ለውጥ ህዝቡ ስላየ የሚያመው ካለ እየታመመ ይቀጥላል እንጂ ለውጡ ይቀጥላል ።

የምንጊዜም ጀግና የህዝብ ልጅ ትንታጉ መሪ !🙏🙏🙏

በኢትዮጵያዊነትህ የምታምን ከሆነ ፣ በአስተሳሰብህ ከመንደርተኞች ተነጥለህ ውጣ እና ፣ ከፍ ብለህ ብረር ፣ እንዳትጠጋቸው🧐።በገጠመህ ሁሉ አትደንግጥ ፤ ለሁሉም ነገር መልስ አትስጥ ፤ ዝምብለ...
22/07/2025

በኢትዮጵያዊነትህ የምታምን ከሆነ ፣ በአስተሳሰብህ ከመንደርተኞች ተነጥለህ ውጣ እና ፣ ከፍ ብለህ ብረር ፣ እንዳትጠጋቸው🧐።በገጠመህ ሁሉ አትደንግጥ ፤ ለሁሉም ነገር መልስ አትስጥ ፤ ዝምብለህ ጉዞህን ቀጥልና ጠላትህን የሚያስጨንቅ ከፍታ ላይ ውጣ።🙌

ሰላምህ ይብዛ!!🕊️

ደህና ሁን ወገኔ!!💪🏾

#ዳሮስ🙏🏽

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Saro Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Saro Media Network:

Share