17/04/2026
የቁሕዴፓ የክልልን መዋቅር የመናቅ አደገኛ አካሄድ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን ስር የሚገኘው የቁጫ ምርጫ ክልል የራሱ የሆነ የጸጥታ መዋቅርና የክልል ፖሊስ ኃይል እያለው ቁሕዴፓ (የቁጫ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ) የፌዴራል ፖሊስን በቀጥታ አስገባለሁ ማለቱ ለክልሉ መንግሥትና ለሕዝብ ጸጥታ መዋቅር ያለውን ከፍተኛ ንቀት ያሳየበት ነው።
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ሥርዓት መሠረት የአንድን አካባቢ ሰላምና ጸጥታ የማስከበር ቀዳሚ ኃላፊነት የክልሉ መንግሥት ነው።
የክልሉ የጸጥታ መዋቅር ከአቅሜ በላይ ነው የሚል ጥያቄ ሳያቀርብና በሕግ አግባብ የፌዴራል ኃይል ሳይጠየቅ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ የፌዴራል ፖሊስን ማስገባት መፈለጉ ከክልሉ መንግሥት በላይ ነኝ የሚል ግብዝነት ነው። ይህ ድርጊት የክልሉን ፖሊስ ክብርና ብቃት ዝቅ አድርጎ የሚመለከት ነው።
ቁሕዴፓ ለክልሉ አስተዳደርና ሕግ የማይገዛው ለምንድነው? መልሱ ግልጽ ነው በክልሉ ሕጋዊ አሠራር ውስጥ ሆኖ በሰላማዊ መንገድ መወዳደር ስላቃተው የፌዴራል ኃይልን እንደ ጋሻ በመጠቀም አካባቢውን ለመረበሽና የሁከት ቀጠና ለማድረግ እያሴረ ይገኛል።
የክልሉን ፖሊስ ገፍቶ የፌዴራል ፖሊስን መጥራት፣ በሕዝብና በመንግሥት መካከል ያለውን መተማመን ለማፍረስ የታቀደ የፖለቲካ ደባ ነው።
ፓርቲው የጸጥታ ስጋት የለም እያለ በሌላ በኩል የፌዴራል ፖሊስ ካልጠበቀኝ ማለቱ የንግግርና የተግባር ቅራኔውን ያሳያል። ይህ የሚያሳየው ፓርቲው የሕዝብ ድጋፍ እንደሌለውና በኃይል ታጅቦ የፍርሃት ድባብ ለመፍጠር መዘጋጀቱን ነው።
ሰላማዊ ምርጫ የሚካሄደው በሕዝብ አመኔታና በሕጋዊው የክልል የጸጥታ መዋቅር እንጂ በፓርቲ ፍላጎት በሚዘወር የኃይል ስምሪት አይደለም።
ቁሕዴፓ የክልሉን መንግሥት ሕጋዊ ሥልጣንና የጸጥታ መዋቅር በመናቅ የሚያደርገውን ይህን የጥፊ ፖለቲካ በጽኑ እንቃወማለን።
የክልሉ ፖሊስ የሕዝቡን ሰላም ለማስከበር ብቃትና ዝግጁነት እያለው ሆን ተብሎ የሚደረግ የፌዴራል ኃይል ጣልቃ ገብነት ፍፁም ተቀባይነት የሌለውና ለቀጣይ ቀውስ መነሻ የሚሆን ተግባር ነው።
ቁሕዴፓ ሆይ ለምርጫው የምትገዛው በክልሉ ሕግና መዋቅር እንጂ የራስህን መንግሥት በክልሉ ላይ ለመመሥረት በምታደርገው ሕገ-ወጥ ጉዞ አይደለም።
የክልሉን ፖሊስ መናቅ ሕዝቡን መናቅ ነው የሰላምበርን ሰላም ለማደፍረስ የምታደርገው የኃይል ፖለቲካ በሕዝብ ትግል ይከሽፋል