21/04/2026
እባካችሁ የምንችለውን ሁሉ እናድርግ እና የሳቂታውን ሳቅ እንመልስ!!!!!!!!!!
ኢትዮጵያዊያን ድኜ እስክነሳ ልጆቼን ደግፉልኝ!💔🙏 #ሁላችንንም በሳቅ ሲያዝናና የቆየው ተወዳጁ ኮሜዲያን በረከት በቀለ (ፍልፍሉ) በአሁኑ ወቅት በጤና እክል ምክንያት በሆስፒታል አልጋ ላይ ሆኖ ለሁላችሁም የሚከተለውን ልብ የሚነካ መልዕክት አስተላልፏል።
ፍልፍሉ ካለፈው እሁድ ጀምሮ ከልጆቹ ጋር በዓልን ለማሳለፍ ቢመኝም፣ በህመሙ ምክንያት ሳይሳካለት ቀርቷል።
"አሁን መቆምም ሆነ መራመድ አልችልም። ካልተንቀሳቀስኩና ካልተራመድኩ ልጆቼን ማስተዳደር አልችልም" የሚለው ስጋቱ የሁላችንንም ልብ ይሰብራል።
ዛሬ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ፍልፍሉ የሚገኝበት ሆስፒታል በመሔድ ጸሎት አድርገውና ለመላው ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ምእመናን አግዙት የሚል መልእክት አስተላልፈዋል።
በአሁኑ ወቅት በዶክተሮች ክትትል ስር ሆኖ የሁላችንንም ድጋፍና ፀሎት ይሻል።ፍልፍሉን በገንዘብ ለመደገፍም ሆነ በፀሎታችሁ ለማሰብ ለምትፈልጉ ከታች ባለው አካውንት መደገፍ ይቻላል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ CBE ፦ 1000374461315
በረከት በቀለ
እኛም ፈጣሪ ለተወዳጁ አርቲስታችን ፍጹም ጤናን እንዲሰጠውና ወደ ልጆቹና ወደ ስራው እንዲመልሰው እንመኛለን። ይህን መረጃ በማጋራት (Share በማድረግ) ለደጋፊዎቹ እና ለወዳጆቹ እናድርስ።
#በረከትበቀለ #ፍልፍሉ #ጤና #ኢትዮጵያ #ድጋፍ #እርዳታ