አርቲስት መሆን ለሚፈልጉ

አርቲስት መሆን ለሚፈልጉ training and support

የጥበባት ስራ ሰርተው ህዝብን ለማገልገልና የራሳቸውን የጥበብ ክህሎት መሸጥ ለሚፈልጉ እናሠለጥናለን! እናማክራለን! ወጥታማ እናደርጋለን! የሁነት ዝግጅት ስራዎችን በፍፀም ህጋዊ ማእቀፎች እንሰራለን! የማማከር አገልግሎት ለማፈልጉ ገንዘብና ጊዜዎን ሳያባክኑ መስራት ስፈለጉት ቀርበው ቢያማክሩን ውጤታማ እንደምናደርጎ አንጠራጠርም።

የጥላቻ ንግግር የወንጀል ተጠያቂነት~~~~~~🎤ማንኛውም ሰው የጥላቻ ንግግርን በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በ...
06/06/2025

የጥላቻ ንግግር የወንጀል ተጠያቂነት
~~~~~~
🎤ማንኛውም ሰው የጥላቻ ንግግርን በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለ ነው፡፡

🎤የተከለከለውን የጥላቻ ንግግር ያደረገ እንደሆነ እስከ ሁለት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት ወይም ከብር 100ሺ ያልበለጠ መቀጮ ይቀጣል፡፡

🎤በጥላቻ ንግግሩ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ እንደሆነ ቅጣቱ ከአንድ አመት እስከ አምስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት ይሆናል።

👉የሐሰት መረጃን ማሰራጨት ስለመከልከሉ
ማንኛውም ሰው የሐሰት መረጃን በአደባባይ ስብሰባዎች በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በጽሁፍ፣ በምስል፣ በድምጽ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለ ተግባር ነው፡፡

ማንኛውም ሰው ክልከላ የተደረገበትን ተግባር የፈጸመ እንደሆነ እስከ አንድ አመት በሚደርስ በቀላል እስራት ወይም ከብር ፶ሺ ባልበለጠ መቀጮ ይቀጣል፡፡

🎤የጥላቻ ንግግር ወይም የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት ወንጀሉ የተፈጸመው ከአምስት ሺ በላይ ተከታይ ባለው የማህበራዊ ሚዲያ ገጽ ከሆነ ወይም በብሮድካስት አገልግሎት ወይም በየጊዜው በሚወጣ የህትመት ውጤት ከሆነ ቅጣቱ እስከ ሶስት አመት የሚደርስ ቀላል እስራት እና ከብር ፻ሺ ያልበለጠ መቀጮ ይሆናል፡፡

🎤ሐሰተኛ መረጃ በመሰራጨቱ ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት የተፈጸመ ከሆነ፣ ሁከት ወይም ግጭት የተከሰተ እንደሆነ ከሁለት እስከ አምስት አመት በሚደርስ ቀላል እስራት ይሆናል።

🎤በጥላቻ ንግግር ወይም በሐሰተኛ መረጃ ወንጀል መፈጸም ምክንያት በግለሰብ ወይም በቡድን ላይ ጥቃት ያልተፈጸመ ወይም ያልተሞከረ ከሆነ፣ ሁከት ወይም ግጭት ያልተከሰተ እንደሆነ እና ጥፋተኛውን ለማረም የተሻለ ነው ብሎ ሲያምን ፍርድ ቤቱ በእስራት ምትክ የግዴታ የማህበረሰብ አገልግሎት ስራን በአማራጭ ቅጣትነት ሊወስን ይችላል።

👉የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም፦

🖌"ንግግር” ማለት በቃል፣ በጽሑፍ፣ በምሥልና ሥዕል፣ በቅርጻ ቅርጽ እና በሌሎች ተመሳሳይ መንገዶች መልእክትን የማሰራጨት ተግባር ነዉ፣

🖌"የጥላቻ ንግግር" ማለት በአንድ ሰው ወይም በተወሰነ ቡድን ማንነት ላይ ያነጣጠረ፣ ብሔርን፣ ብሔረሰብንና ህዝብን፣ ሃይማኖትን፣ ዘርን፣ ጾታን ወይም አካል ጉዳተኝነትን መሰረት በማድረግ ሆን ተብሎ ጥላቻን፣ መድሎን ወይም ጥቃትን የሚያነሳሳ ንግግር ነው፣

🖌"ሐሰተኛ መረጃ" መረጃው ሐሰት የሆነና የመረጃውን ሐሰተኝነት በሚያውቅ፣ ወይም መረጃውን የሚያሰራጨው ሰው ካለበት አጠቃላይ ሁኔታ አንጻር የመረጃውን እውነተኝነት ለማጣራት በቂ ጥረት ሳያደርግ የሚሰራጭ ሁከት ወይም ግጭት የማስነሳት፣ ወይም ጥቃት እንዲደርስ የማድረግ ዕድሉ ከፍ ያለ ንግግር ነው፣

🖌"ብሮድካስት ማድረግ" ማለት በሬዲዮ ወይም በቴሌቪዥን ሥርጭት ማድረግ ነው፣

🖌"መድሎ" ማለት ብሔርን ብሔር ብሔረሰብን ህዝብን ሃይማኖትን ዘርን ፆታን አካል ጉዳተኝነትን ወይም ሌሎች በህግ የተጠበቁ ልዩነቶችን መሰረት በማድረግ የሚፈጸም የማግለል ተግባር ነው፤

🖌"ጥቃት" ማለት በግለሰብ ወይም በቡድን አባላት ንብረት፣ አካል ወይም ሕይወት ላይ የሚፈጸም ጉዳት ነው፣

🖌"ማሰራጨት" ማለት ንግግርን በማናቸውም መንገዶች ለብዙ ሰዎች እንዲደርስ ማድረግ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያ ላይክ ማድረግና ታግ ማድረግን አያካትትም፣

🖌"ማህበራዊ ሚዲያ" ማለት ሰዎች መልዕክት ለመለዋወጥ ትስስር ለማዳበር ሀሳብ ለመጋራት የሚጠቀሙበት በኢንተርኔት አማካኝነት በአንድ ጊዜ ከአንድ በላይ ለሆኑ ሰዎች መረጃ የሚደርስበት፣ ወይም ማህበራዊ መስተጋብር የሚስተናገድበት መንገድ ነዉ፣

🖌"የህትመት ሚዲያ" ማለት ለህዝብ ስርጭት የተዘጋጀ ማንኛውም የህትመት ወጤት ነው፣

🖌"ማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት የሚሰጥ ድርጅት" ማለት የማህበራዊ ሚዲያ አውታርን ወይም መድረክን ለተጠቃሚዎች የሚያደርስ ድርጅት ነው።

ብዙዎችን ሲያመሰግን ኖሮ አንዳችንም በልኩ ያላመሰገነው ሰው***************************************************          በኢትዮጵያ ትያትር ታሪክ ውስጥ ከብ...
30/05/2025

ብዙዎችን ሲያመሰግን ኖሮ አንዳችንም በልኩ ያላመሰገነው ሰው
***************************************************
በኢትዮጵያ ትያትር ታሪክ ውስጥ ከብዙ ትልልቅ ባለውለታ ዎቻችን ጎን በዚሀ ዘመን በበቂ ያልተነገረለት ሰው ተፈራ ወርቁ ነው ። እኛም እንደ ጓደኛ ብቻ እያየነው ሳንዘምርለት ቀረን ። ይሁንና ስራው እየዘመረለት አለ ።

ላለፉት 25 ዓመታት ከኢትዮጵያ ኪነጥበብ ( በተለይም ከሙዚቃና ትያትር ) ጎን አለ ። ብዙዎችን ከጥበብ ስራቸው ጋር ለአደባባይ አብቅቷቸዋል ። ለእኔም " ሩብ ጉዳይ " እና " ሰዓት እላፊ " የተባሉ ተውኔቶቼን ለሕዝብ አቅርቦልኛል ። በ " ሩብ ጉዳይ " ትያትርን ከተቀመጠበት አቧራውን አራግፎ ሁላችንንም እርካታ እንድናገኝበት ፣ ገንዘብ እንድንሰራበት ፣ በታሪክ እንድንደምቅበት ያደረገን ባለውለታችን ነው ተፈራ ወርቁ ። ቁጭታችንን የተወጣልን ሰው ነው ። ከትያትር ቤቶች ስንገፋ መሸሻችን ነው ።

ካሜራ ባልቀረጻቸውና ለአደባባይ ባልበቁ መልካምነቶቹ ስመጥር ነው ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር " በጀት አጠረኝ " ብሎ ያቆመውን " የቴዎድሮስ ራዕይ " ትያትር ተፈራ ወርቁ ባይሆን ማንም ለመድረክ አያበቃውም ። የፊታችን ሰኞ ግንቦት 25/17 በሀገር ፍቅር ቴአትር በልዩ ፕሮግራም ለሕዝብ የሚያደርሰው የውድነህ ክፍሌ ድርሰት የሆነው " ደጋግ ሰይጣኖች " ከትጋቶቹ አንዱ ነው ። የትያትሩ አዘጋጅና ፕሮዲዩሰር ነው ተፈራ ። ሁሌም ብርታቱን ፣ መልካምነቱንና አይታክቴነቱን በልባችን የምናመሰግነው ተፈራ ወርቁ በአደባባይ የሚመሰገንበት ቀን ይመጣል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።

ሰኞ በ11:00 ሰዓት ሀገር ፍቅር ቴአትር እንገናኝ ።
Tewodros Teklearegay

28/05/2025

ታላቁ ፈላስፋ ሶቅራጠስ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር፦“አህያ ቢመታኝ ልከሰው ነው? ወይስ ልሰድበው? አልያም ደግሞ ልረገጠው?”ሁሌም ቢሆን እያንዳንዱን ክርክር ለማሸነፍ ከመነሳታችን በፊት...
17/05/2025

ታላቁ ፈላስፋ ሶቅራጠስ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር፦

“አህያ ቢመታኝ ልከሰው ነው? ወይስ ልሰድበው? አልያም ደግሞ ልረገጠው?”

ሁሌም ቢሆን እያንዳንዱን ክርክር ለማሸነፍ ከመነሳታችን በፊት አዕምሮና ጉልበታችንን ለምን እንደምናባክን እራሳችንን መጠየቅ አለብን።ጨዋታውን ለይቶ ያወቀ አሸናፊነት ራሷ ትመርጠዋለች። ከማይመጥነን ጦርነት መታቀብ የድል ጀንበር ጭላንጭል ነው። ድንቁርና ትጮኻለች ጥበብም ዝም እንዳለች ነው።ማንም ሰው ከስድብና ከጩኸት በቀር የሚያቀርበው ነገር ከሌለው በጣም ሃያሉ ምላሽ ዝምታ ነው።

ግጭት እና ፀብን ወደ ሚፈልግ ሰው ደረጃ አታዘንብሉ።እውነተኛ ብልህነት እራሱን እሳት አይለኩስም፤ በቀላሉ ያበራል…
#ከፌስ ቡክ መንደር የተገኘ መረጃ
**********************
በጥበቡ አለም አስቸጋሪዎቹ ፣ የጥበቡ አርካሽና ዘባራቂዎች ያለ ብቃትና ችሎታቸው ወደ ጥበብ መጥተው የሚዘባርቁት ናቸው። ሁሉም ዋጋ ከፍሎ ተምሮ ተመራምሮ በጥበቡ አለም እየሰራ ያለ ሙያው ከጋጥወጦች ለማዳን ቆርጦ መስራት ይኖርበታል።

10/05/2025

የሀገራችን የኪነ-ጥበብ ሙያ ውድቀት ዋና ችግር የሙያው ብቃት የሌላቸው ፣ በዘርፉ በበቂ ያልተማሩና ስነምግባር የሌላቸው ገበያውን ማጥለቅለቃቸው ነው!እነዚህ ያለ ብቃታቸው የጥበቡን አለም የወ...
07/05/2025

የሀገራችን የኪነ-ጥበብ ሙያ ውድቀት ዋና ችግር የሙያው ብቃት የሌላቸው ፣ በዘርፉ በበቂ ያልተማሩና ስነምግባር የሌላቸው ገበያውን ማጥለቅለቃቸው ነው!
እነዚህ ያለ ብቃታቸው የጥበቡን አለም የወረሩት ደግሞ ለተመልካች ደንታ የላቸውም። የነሱ ጥረት እራሳቸውን ማሳየት ነው።

የኪነ-ጥበባት ሙያተኞች ከደንበኞቻቸው ገንዘብ ለመቀበል የሚሸጡላቸው አገልግሎት/ምርት ሊኖራቸው ይገባል። ምርቱ/አገልግሎቱ የገዢውን ህይወት የሚለውጥ መሆን አለበት። ዋጋ የሚያወጣ መሆን አለበ...
06/05/2025

የኪነ-ጥበባት ሙያተኞች ከደንበኞቻቸው ገንዘብ ለመቀበል የሚሸጡላቸው አገልግሎት/ምርት ሊኖራቸው ይገባል። ምርቱ/አገልግሎቱ የገዢውን ህይወት የሚለውጥ መሆን አለበት። ዋጋ የሚያወጣ መሆን አለበት። ያለዚያ እኔ ጥበብ ደስ ስለሚለኝ ፣ ተሰጦዬ ስለሆነ እያሉ ብቻ የፈለጉትን እየሰሩ ለተመልካች/ደንበኛው ማቅረብ የሚሞክሩ መክሰራቸው አይቀሬ ነው። የሀገሪቱን የጥበብ ገበያ ያከሰረውና የጥበብ ሰው ቁም ነገር ያለው ተደርጎ እንዳይወሰድ ያደረገው ይህ ነው። አንዳንድ የጥበብ ሰው ነኝ የሚሉ በአደባባይ ወጥተው እውቀታዊ ያልሆነ ነገር ተናግረው እራሳቸውንም ሙያውንም የሚያሳንሱት ለዚሁ ነው።
እርሶ ምን አይነት አርቲስት ኖት! ምን አይነት አርቲስትስ መሆን ይፈልጋሉ?

06/05/2025


06/05/2025

በኢትዮጵያ ፊልምና ቴአትር ውስጥ በዚህ ዘመን በዘርፉ እየሰሩ በፊልምና ቴአትር ብቻ አስተማማኝ ኑሮ የሚኖሩ አሉ?
ከሌሉ ለምን ይመስላችኋል???

01/05/2025

ሰልፉ
(በእውቀቱ ስዩም)

እንኳን ለላብአደሮች ቀን አደረሳችሁ !

አንዱ ወዳጄ በቀደም ስናወራ ፤ “የኪነጥበብ ባለሙያዎች ላብ አደር ሊባሉ አይችሉም ፤ ላብአደር ማለት ከሞላ ጎደል ጉልበት የሚጠይቅ ስራ የሚሰራ ነው”አለ፤

ይህንን ስሰማ ብልጭ አለብኝ፤

“ስማ! ድሮ የዳህላክ ባንድ ሙዚቃ መሳርያ ተጫዎቾችን አይተሀቸዋል? ከሰላሳ አመት በፊት የነበረው ጊታርኮ ከሞፈር ይከብዳል፤ ዘፋኞችን በተመለከተ ከካሳ ተሰማና ከሜሪ አርምዴ በቀር ያለው ዘፋኝ ሁሉ እንዳለ ላብአድር ነው፤ ጥላሁን ገሰሰ “እይዋት ስትናፍቀኝ የሚለውን ዘፍን ሲዘፍን የሚያወጣው ኢነርጂኮ ወደ ጉልበት ቢመነዘር ማራቶን ያስሮጣል” በማለት መለስሁ፤

“አሁን አንተም ላብ አደር ነኝ ትላለህ?”

“ዠለስ! እኔኮ አንድ የግጥም ሀሳብ ለማግኘት ከቀበና አዲሱ ገበያ ድረስ በእግሬ የምኳትን ሰው ነኝ፤ ላብአደር ለመባል የግድ ብብቴን ያበስኩበትን ያደፈ ፎጣ ማሳየት አለብኝ እንዴ?! እንከባበር እንጂ!”


ኤፍኤም አዲስ ስራ የጀመረ ሰሞን ትዝ ይለኛል ፤ ብዙ ዝግጅት ስላልነበረ አብዛኛው የጣቢያው ጊዜ የሚሸፈነው ለሰፊው ህዝብ ዘፈን በመጋበዝ ነበር፤ ከዚያ በፊት በነበረው የሬድዮ ታሪክ ዘፈን የሚመርጡት ጋዜጠኞች ነበሩ፤ ድንገት ደጄ የሚባል ባለሙያ መጣ፤ ዲጄ" ሚን" የሚባል ዝነኛ ልጅ ነ ከተፍ አለ፤ ዘፈን በመምረጥ ብቻ ሳይሆን ዜማ በመከለስ፥ የዘፋኞችን ታሪክና ውሎ አስውቦ በመተረክ ታዋቂ ሆነ፤

ዲጄው በህዝብ ዘንድ በተወደደበት ሰሞን ፥ ከሬድዮው ጣቢያው ባለስልጣኖች ጋራ መስማማት ስላልቻለ ስራ ለቀቀ፤

የጣቢያው ባለስልጣኖች ፥ የህዝቡ ተቃውሞ ሲበረታባቸው ፥ይቅርታ ጠይቀው፥ ደመወዝ ጨምረው ወደ ቦታየ ይመልሱልኛል ብሎ ተስፋ አድርጓል፤

ከሁለት ቀን በሁዋላ ዲጂ ሚን፥ ለስራ ባልደረባው ስልክ ደወለለት፤

“ እኔ መልቀቄ ለህዝብ ከተነገረ በሁዋላ በመዲናይቱ ያለው ሁኔተ እንዴት ነው?”

“ ከትናንት ጀምሮ ብዙ ሰው የጣቢያችንን በር ላይ ተሰልፎ ነበር”
አለ ባልደረባው፤

ዲጄን ሚን፥ በድል አድራጊነት ፈገግ ብሎ የሚከተከውን ጥያቄ አስከተለ፤

“ደጂውን መልሱልን የሚል የተቃውሞ ሰልፍ ነው?”

“የተቃውሞ ሳይሆን የስራ ሰልፍ ነው፤ ባንተ ቦታ ለመቀጠር ማመልከቻ የሚያስገቡ ሰዎች ጣቢያችንን ሲያጨናንቀት ነው የዋሉት “

ምን ለማለት ነው ጓዶች! እኛ የምንማረርበትን ስራ በናፍቆትና በጉጉት የሚጠብቁ መአት ሰዎች በዙርያችን አሉ ፤
በእውቀቱ ስዩም
https://www.facebook.com/share/1LXPuqyN1f/

 #
29/04/2025

#

Address

Djibouti Street
Addis Ababa

Telephone

+251988708090

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አርቲስት መሆን ለሚፈልጉ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share