20/04/2026
ክቡር አምባሳደር አቶ ሬድዋን ሁሴን የሚከተለውን
መልዕክት በፌስበቡክ ገፃቸው ላይ አጋርተዋል
"የግል ሀዘንና ደስታ ፣ ሳቅና ለቅሶ ፣ መታመምና መዳን ሁልጊዜ ለገበያ መቅረብ አለበት ብዬ አላምንም። ግን ደሞ አደባባይ የሚያውል ስምሪት ላይ ያለ ሰው ከፊል ህይወቱ ለህዝብ ዕይታና አስተያየት ክፍት መሆኑ የግድ ነው። እናም በዋነኝነት ሰሞኑን ወዳጅና ዘመድ፣ ቢያንስ ኢትዮጵያዊ ስለሆንን አሳሰበን፣ እንደ ሰው ምን ተፈጠረ? በሚል የተጨነቁትን ታሳቢ በማድረግ መርጃ ባጋራ በማለት የሚከተለውን ግልፅ ማድረግ ፈለኩ። በዚያውም የመጥፎ ምኞትና ሀሰትን መሰረት መረጃ በማጥራት አስታክኬ ጎሸም ባደርግ ደግኛ ነው ብዬ።
ከሁለት ሳምንታት በፊት በሀገራዊ ጉዳይ የሚመክር ስብሰባ አስተናግደን ለምሳ እንዳረፍን ንፋስ ለመከላከል የተጋረደ የእንጫት አካፋይ ( Partition Wall ) ሚዛን ስቶ ሲወድቅ አናቴ ጋርና ትንሽ ገባ ብሎ አገኘኝ። ስንጥቁ መሰፋት ስለነበረበት ሀኪሞች በከፊል ላጩት። እኔ ደሞ ሙሉውን ቢሆን ይሻላል ብዬ እስከሚደርቅ አነሳሁት።
እንደልጅነቴ ተመልጬ ሳየው አልጠላሁትም። ወዳጆችም እንዲያውም ሸጋ ነው አሉኝ። በተመልካች አስተያየት ተበረታትቼ ትንሽ ደሞ በአዲስ መልክ ልሞክረው ብዬ ዘለቅኩበት።
የሆነው ይኽው ነው። የታከምኩትም አሚን ሆስፒታል ነው።እናማ እንኳን ለህክምና ለስራም ወደ ውጭ ሀገር አልወጣሁም። ምንም ያልተባለውም ምን አዲስ ነገር አለ በሚል ነው። ለማንኛውም ለተጨነቁት ምስጋናና አክብሮቴ ይድረስ።"