Liveaddis-ላይቭ አዲስ

Liveaddis-ላይቭ አዲስ We take care of your hassle and minimize your budget and you focus on your business.

Events and Entertainment
Live Addis Events and Entertainment organizes flawless events carefully and professionally designed based on your specific needs and wants. ምን ዓይነት ፕሮግራም ለማዘጋጀት አስበዋል? ላይቭ አዲስ ኢቭንት የእርሶን ፍላጎት ፣ በጀት እና ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ከሚያስቡት በላይ ያማረ እና የተሳካ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት የታወቀ ኢቭንት አዘጋጅ ድርጅት ነው፡፡ እርስዎ ስራዎ ላይ ትኩረት ያድረጉ እኛ ከ ሀ እስከ ፐ ያለውን የፕሮግራሙዎን ጣጣ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ብቃት ባላቸው ባለሞያዎች ጥንቅቅ አድርገን መስራት

ብቻ ሳይሆን ወጪዎን ጭምር በመቀነስ ከጭንቀት እና ውጥረት እንገላግሎታለን፡፡ ለማንኛውም ፕሮግራም ላይቭ አዲስ ኢቭንትን ያማክሩ፡፡ ለሠርግ ፣ ለልደት ፣ ለሙዚቃ ኮንሰርት ፣ ለምርቃት ፣ ለቤቢ ሻወር ፣ ወዘተ ላይቭ አዲስ ኢቨንት ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡ ምን እያሳሰቦት ነው? ዲኮር ፣ ዲጄ ፣ ላይቭ ባንድ ፣ ታዋቂ እና ዝነኛ ዘፋኞች ማግኘት ፣ የተዋበ አዳራሽ ፣ ተወዛዋዥ ፣ አጃቢ ፣ ባህላዊ አልባሳት ፣ ... ላይቭ አዲስ ኢቭንት ሁሉም ፍላጎትዎን በዝርዝር እና በጥንቃቄ ተረድቶ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡

ለወደብ ኪራይ የወጣው ከ12 በላይ ህዳሴ ግድቦችን ማስገንባት ይችል ነበር ተብሏል።📌በዘርፉ በርካታ ምርምሮችን የሠሩት የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ተመራማሪ አቶ ሰለሞን ተፈራ ለጋዜጣ ፕላስ...
20/09/2025

ለወደብ ኪራይ የወጣው ከ12 በላይ ህዳሴ ግድቦችን ማስገንባት ይችል ነበር ተብሏል።

📌በዘርፉ በርካታ ምርምሮችን የሠሩት የአዲስ አበባ አመራር አካዳሚ ተመራማሪ አቶ ሰለሞን ተፈራ ለጋዜጣ ፕላስ ዘጋቢ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ ላለፉት 36 ዓመታት ለወደብ ኪራይ ለጅቡቲ ያወጣችው ከ12 በላይ የህዳቤ ግድቦችን ይሰራ ነበር ብለዋል።አቶ ሰለሞን እንዳሉት:-

📌ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይ በዓመት ሁለት ቢሊዮን ዶላር ትከፍላለች፤
📌ባለፉት 36 ዓመታትም ለጅቡቲ 72 ቢሊዮን ዶላር ከፍላለች ብለዋል፡፡

📌ይህም ህዳሴ ግድብን ለመገንባትከወጣው ወጪ አንጻር ሲታይ ሀገሪቱ ባለፉት 36 ዓመታት ለወደብ ኪራይ ያወጣችው ዶላር ቢሰላ ከ12 በላይ ህዳሴ ግድቦችን ማሰራት የሚያስችል ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

📌ኢትዮጵያ ለወደብ ኪራይ የከፈለችው 72 ቢሊዮን ዶላር ሀገር ውስጥ ኢንቨስት ቢደረግ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን ገንብቶ ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ይበልጥ ያረጋግጥ ነበር ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በሴቶች የተደረሱ መፅሐፍት ተወገዱ‼የአፍጋኒስታኑ ታሊባን በሴቶች የተደረሱ  መጽሐፍትን ከአገሪቱ ዩንቨሪሲቲዎች አስወገደ።የታሊባን መንግስት በሴቶች የተጻፉትን መጽሐፎች  ከማስወገድ ባሻገር ስ...
20/09/2025

በሴቶች የተደረሱ መፅሐፍት ተወገዱ‼

የአፍጋኒስታኑ ታሊባን በሴቶች የተደረሱ መጽሐፍትን ከአገሪቱ ዩንቨሪሲቲዎች አስወገደ።

የታሊባን መንግስት በሴቶች የተጻፉትን መጽሐፎች ከማስወገድ ባሻገር ስለሰብዓዊ መብት እና ጾታዊ ጥቃት ማስተማርንም ህገ ወጥ ብሎ ፈርጇል።

ሴፍቲ ኢን ዘ ኬሚካል ላቦራቶሪ የተሰኘውን ጨምሮ 140 መጽሐፎች ከ680ዎቹ መካከል የታሊባንን ፖሊሲ የሚጥሱና ከሸሪዓው በተጻጻሪ ሆነው የተገኙ ናቸው ተብሏል።

በተጨማሪም ዩንቨሪሲቲዎች 18 የትምህርት ዓይነቶችን እንዳያስተምሩ ተከልክለዋል።

ከስርዓቱ ፖሊሲዎች ያፈነገጡ ነቸው ያላቸውን ስራዎች የከለከለው ታሊባን ከአራት ዓመታት በፊት ነበር ዳግም የካቡል ፖለቲካን የተቆጣጠረው።

የአፍጋኒስታን አስተዳደር ውሳኔ በርካታ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችልም ተጠቁሟል።

በተለይም ከስድስተኛ ክፍል በላይ ትምህርት እንዳያገኙ ለተከለከሉት የአፍጋኒስታን ሴቶች ተጨማሪ ፈተና ይሆንባቸዋል ተብሏል።

ታሊባን የሴቶችን መብት በአፍጋኒስታን ወግ ባህልና በእስላማዊ ስርዓት መሰረት እንደሚያከብር አሳውቋል።

ታሊባን የአሽራፍ ጋኒን መንግስት እና የአሜሪካን ኃይሎች ከካቡል ሲያስወጣ ከቀደመው እያስተዳደሩ የተሻለ ሀሳብ ያመጣል የሚል ተስፋ ተጥሎበት ነበር።
ዘገባው የቢ ቢ ሲ ነው።

16/09/2025

ውይ 9ኛው ሺ 😀😀
ጋሽ ብሬ ግን 👍👍 ይገባቸዋል

"ከግድቡ ወደ ወደቡ"ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት ዛሬ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።ከተያዙ መፈክሮች መካከል:-📌"ከግድብ ወደ ወደብ!...
14/09/2025

"ከግድቡ ወደ ወደቡ"

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቅቆ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት ዛሬ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
ከተያዙ መፈክሮች መካከል:-
📌"ከግድብ ወደ ወደብ!
📌በተባበረ ክንድ የኢትዮጵያ ጉዞ እውን ይሆናል!
📌የህዳሴ ግድብ የአሸናፊነት አክሊል ነው!
📌ግድባችን የታሪክ ስብራት መጠገኛ ሆኗል!
📌በራሳችን አቅም የአፍሪካ ምሳሌ መሆን ችለናል!
📌በህብረት ችለናል!
📌የሚደግም ድል በሚጨበጥ ብስራት!
📌ግድባችን የልፋታችንና የጠብታችን ማብሰሪያ ነው!
📌የጉባ ራዕያችን የቀጣይ ድላችን አይቀሬ ነው!
📌አባይ ከቁጭት እናቶች ከእንጨት ነጻ ሆነዋል!
📌መጭው ትውልድ ዳግማዊ አድዋን በህብረት ይዘክራል!" የሚሉት ይገኝበታል።

ፕሬዝደንት ታዬ አስቀስላሴና ከንቲባ አዳነች አቤቤ የታላቁ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅን በተመለከተ መልዕክት አስተላልፈዋል።
Via-ዋሱመሐመድ

ከ51 ዓመታት በፊት መስከረም 2 በዚህ ቀን ምን ተፈፅሟል?📌መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም አፄ ኃይለሥላሴ ከዙፋናቸው ወረዱ📌መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም የደርግ አባላት 13 ሆነው ወደ ቤ...
12/09/2025

ከ51 ዓመታት በፊት መስከረም 2 በዚህ ቀን ምን ተፈፅሟል?

📌መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም አፄ ኃይለሥላሴ ከዙፋናቸው ወረዱ

📌መስከረም 2 ቀን 1967 ዓ.ም የደርግ አባላት 13 ሆነው ወደ ቤተ-መንግሥት ሄዱና ጃንሆይ የአገዛዝ ዘመናቸው ማብቃቱን አረዷቸው፡፡ የደርግ አባላት ቤተ-መንግሥት ደርሰው ንጉሱን አስጠሯቸው፡፡ ንጉሱም በዝግታ ከፎቅ ላይ ወርደው በዙፋናቸው ላይ ሲቀመጡ የደርግ አባላት ደነገጡ፡፡

📌ሻምበል ደበላ ዲንሳ ደርግ የወሰነውን የውሳኔ ሃሳብ አነበቡ … ‹‹ … ለሀገርና ለህዝብ ደህንነት ሲባል በዛሬው ዕለት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ወርደዋል፤ ለደህንነትዎ ሲባልም አስተባባሪው ኮሚቴ ወዳዘጋጀልዎ ቦታ እንዲሄዱ ተወስኗል …›› የሚል ይዘት ያለው ደብዳቤ አነበቡ፡፡ ሻምበል ደበላ ውሳኔውን አንበበው ሲጨርሱ ንባባቸውን ሲጀምሩ የሰጡትን ወታደራዊ ሰላምታ ደገሙ፡፡

📌ንጉሱም ዝም ብለው ቆዩና መናገር ጀመሩ፡፡ ‹‹ያነበባችሁትን ሰምተናል፤ የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገሥት ስንሆን ስም ብቻ አይደለም፡፡ ቢሆንም በየጊዜው የሚለዋወጠው ነገር ደግሞ ላገር የሚጠቅም ነገር እስካለበት … የኢትዮጵያን ታሪክ ጠብቃችሁ ማልማት ከቻላችሁ የእኛ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃል፤ ካልቻላችሁ የእናንተ ታሪክ ያበቃና የእኛ ይቀጥላል፤ አገራችንንና ሕዝባችንን በምንችለው አገልግለናል፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ እድል የእኛን መወገድ የሚጠይቅ ከሆነ ስራችንን አቁመን ማንኛውንም ነገር ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ‹አሁን ተራው የእኛ ነው› ካላችሁ ኢትዮጵያን ጠብቁ›› በማለት ተናገሩ፡፡

📌… ከዚያም ንጉሱ ውብ በሆነችው ሮልስ ሮይስ መኪናቸው ሳይሆን ባረጀች ሰማያዊ ቮልስ ዋገን መኪና ተጭነው ወደ አራተኛ ክፍለ ጦር ግቢ ተወሰዱ፡፡ያች ቀን 51 ዓመታትን አስቆጠረች።
Via-ዋሱመሐመድ

12/09/2025

መልካም በአል🌼🌼😀

"ነገ ጷጉሜ 2 የጨረቃ ግርዶሽ ይከሰታል" ዶ/ር ሮዳስ   በኢትዮጵያ ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃ ነገ ጳጉሜን 2/2017 ዓ.ም እንደሚታይ የሥነ ፈለግ ባለሙያ መጋቤ ሐዲስ ...
06/09/2025

"ነገ ጷጉሜ 2 የጨረቃ ግርዶሽ ይከሰታል" ዶ/ር ሮዳስ

በኢትዮጵያ ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃ ነገ ጳጉሜን 2/2017 ዓ.ም እንደሚታይ የሥነ ፈለግ ባለሙያ መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ አስታውቀዋል፡፡

በዕለቱ ከምሽቱ 12፡28 መሬት ጨረቃን መከለል ስትጀምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል ብለዋል፡፡

ከነገ እሁድ ምሽት 1፡27 ደግሞ ከፊል ግርዶሹ እንደሚጀምር፣ ከምሽቱ 2፡30 ላይ ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽን ጨምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት መሆኑን መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ተናግረዋል፡፡

ከምሽቱ 3፡11 ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት እንደሚሆን እና ከምሽቱ 3፡52 ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ደም መምሰሏ ማብቂያው እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡

ግርዶሹ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በአፍሪካ፤ አውስትራሊያ እና እስያ የተወሰኑ አከባቢዎች አንደሚታይ በመግለጽ፤ ለ1 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ያህል እንደሚቆይም ጠቁመዋል፡፡

ደመና ከሆነ የመታየት እድል እንደሌለውና ደመና በሌለባቸው አካባቢዎች ግን በግልፅ እንደሚታይ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብቻ የሆነችው ጷጉሜ ወር በድምቀት የምትታይበት ጊዜ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
Via-ዋሱመሐመድ

04/09/2025

😱😱

ወንዶችን እያደኑ በዱላ የሚደበድቡት ሴቶችበሴቶች ላይ በደል የሚፈጽሙ ወንዶችን ካሉበት እያደኑ በዱላ የሚደበድቡት የሴቶች ቡድን ‼ህንድ ውስጥ በሀምራዊ ቀለም ያሸበረቀው የሴቶች ቡድን 'ጉላቢ...
30/08/2025

ወንዶችን እያደኑ በዱላ የሚደበድቡት ሴቶች

በሴቶች ላይ በደል የሚፈጽሙ ወንዶችን ካሉበት እያደኑ በዱላ የሚደበድቡት የሴቶች ቡድን ‼

ህንድ ውስጥ በሀምራዊ ቀለም ያሸበረቀው የሴቶች ቡድን 'ጉላቢ ጋንግ' በሀገሪቱ ውስጥ በሚፈጸም የሴቶች በደል ላይ የራሱን የፍትህ እርምጃ በመውሰድ ትኩረት አግኝቷል። ይህ ቡድን በደል አድራሽ ባሎችን በማደን እና በዱላ በመቅጣት ይታወቃል ነው የተባለው።

ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በሳምፓት ፓል ዴቪ የተመሰረተው ይህ ቡድን በዋናነት የቤት ውስጥ ጥቃቶችን፣ የትምህርት እጥረት እና ያለዕድሜ ጋብቻን በመታገል ይታወቃል ነው የተባለው። የቡድኑ አባላት ደማቅ ሀምራዊ ልብስ በመልበስ እና ዱላ የታጠቁ በመሆናቸው በቀላሉ ይለያሉ ተብሏል።

የጉላቢ ጋንግ አላማ የቤት ውስጥ ጥቃትን መዋጋት ብቻ ሳይሆን፣ ሴቶች በራሳቸው እንዲተማመኑ እና የኢኮኖሚ አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ማገዝ ነው ተብሏል። via-(መነኻሪያ)

27/08/2025

ወይ ጉድ ገና premier league ሳይጀመር እንደዚ. ማሞረት ጥሩ ነው 😀😀

24/08/2025

ፈጣሪየ ሆይ የ አይምሮ ታማሚ ነው በለኝ 🫣🫣

ፍትህ ለ አዲስ አበባ ልጅ 😀😀

24/08/2025

በፎቶ የሚታየው የሳውዲ ዜጋ ማሄር ፋህድ ይባላል።ሰሞኑን መነጋገሪያ ሆኗል።

በነዳጅ ማደያ አቅራቢያ በእሳት የተያያዘ መኪና ሲያይ፣ ብዙ ሰዎች ከፍንዳታ በመፍራት ወደ ኋላ ሲሸሹ፣ እሱ ግን የጀግንነት እርምጃ ወሰደ።

ማሄር በእሳት እየነደደ ባለው መኪና ውስጥ ገብቶ፣ ማደያውን ከእሳት አደጋ ለመከላከል መኪናውን እየነዳ ከአካባቢው በማራቅ አደጋውን ቀንሶታል። ይህ ደፋር ተግባሩም ማደያው በእሳት እንዳይጋይ አድርጓል።

ይህ በቪዲዮ ያዩ የሳውዲ አረቢያ ንጉስ፣ ንጉስ ሰልማን፣ በጀግናውን ተግባር ከመደነቃቸው የተነሳ፣
📌1 ሚሊዮን የሳውዲ ሪያል፣ በኢትዮጵያ ብር ሲመነዘር 36 ሚሊዮን 150 ሺህ ብር ሰጥተውታል።
ይህ ድርጊቱም በአገሪቱ ውስጥ ትልቅ
መነጋገሪያ ሆኗል።

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Liveaddis-ላይቭ አዲስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Liveaddis-ላይቭ አዲስ:

Share

Category