Liveaddis-ላይቭ አዲስ

Liveaddis-ላይቭ አዲስ We take care of your hassle and minimize your budget and you focus on your business.

Events and Entertainment
Live Addis Events and Entertainment organizes flawless events carefully and professionally designed based on your specific needs and wants. ምን ዓይነት ፕሮግራም ለማዘጋጀት አስበዋል? ላይቭ አዲስ ኢቭንት የእርሶን ፍላጎት ፣ በጀት እና ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ከሚያስቡት በላይ ያማረ እና የተሳካ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት የታወቀ ኢቭንት አዘጋጅ ድርጅት ነው፡፡ እርስዎ ስራዎ ላይ ትኩረት ያድረጉ እኛ ከ ሀ እስከ ፐ ያለውን የፕሮግራሙዎን ጣጣ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ብቃት ባላቸው ባለሞያዎች ጥንቅቅ አድርገን መስራት

ብቻ ሳይሆን ወጪዎን ጭምር በመቀነስ ከጭንቀት እና ውጥረት እንገላግሎታለን፡፡ ለማንኛውም ፕሮግራም ላይቭ አዲስ ኢቭንትን ያማክሩ፡፡ ለሠርግ ፣ ለልደት ፣ ለሙዚቃ ኮንሰርት ፣ ለምርቃት ፣ ለቤቢ ሻወር ፣ ወዘተ ላይቭ አዲስ ኢቨንት ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡ ምን እያሳሰቦት ነው? ዲኮር ፣ ዲጄ ፣ ላይቭ ባንድ ፣ ታዋቂ እና ዝነኛ ዘፋኞች ማግኘት ፣ የተዋበ አዳራሽ ፣ ተወዛዋዥ ፣ አጃቢ ፣ ባህላዊ አልባሳት ፣ ... ላይቭ አዲስ ኢቭንት ሁሉም ፍላጎትዎን በዝርዝር እና በጥንቃቄ ተረድቶ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡

😆 አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ ጮቤ ረገጠች​🖋️ ​ትናንት ምሽት በሜክሲኮ በተጀመረው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ፣ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን በመግጠም ውድድሩን በድል ጀምራለች። ጨዋታው በሜዳ ላይ...
12/06/2026

😆 አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ ጮቤ ረገጠች

​🖋️ ​ትናንት ምሽት በሜክሲኮ በተጀመረው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ፣ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን በመግጠም ውድድሩን በድል ጀምራለች። ጨዋታው በሜዳ ላይ ከነበረው ፉክክር ባሻገር፣ በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ክስተት ሆኗል።

​የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ፣ በርካታ አፍሪካዊያን በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይህ ስሜት የመነጨው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚኖሩ ሌሎች አፍሪካዊያን ስደተኞች ላይ በቅርቡ በተፈጠረው “ከሀገራችን ውጡልን” ጥሪ እና ተያያዥ ፀረ-ስደተኞች እንቅስቃሴ ሳቢያ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።

​በሶሻል ሚዲያ አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፣ የደቡብ አፍሪካ ቡድን መሸነፍ በወቅቱ በሀገሪቱ እየታየ ካለው የመገፋፋት ስሜት ጋር በተያያዘ፣ በሌሎች አፍሪካዊያን ዘንድ እንደ አንድ የምሬት መግለጫ እየታየ ነው።

አዲሱ ሰሌዳ 56,000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል‼ 📌የቤት መኪና ሁሉንም አጠቃሎ 59400 ብር ደርሷል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዝርዝሩን...
11/06/2026

አዲሱ ሰሌዳ 56,000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል‼

📌የቤት መኪና ሁሉንም አጠቃሎ 59400 ብር ደርሷል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዝርዝሩን አሳውቋል።

አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ (ታርጋ) መሸጫ ዋጋ እስከ 56000 ብር ዋጋ ተቆርጦለታል ይላል ሰነዱ። የቀረቡት ዋጋዎች የፊትና የኋላ ሰሌዳዎችን እንዲሁም ቫትን (VAT) ያካተቱ መሆናቸውም ተጠቁሟል።

ለግል መገልገያ (የቤት)፣ ለንግድ፣ ለዲፕሎማት፣ ለዕርዳታ ድርጅቶች፣ ለዓለም አቀፍ ተቋማት እና ለልዩ ተንቀሳቃሽ ተሽከርካሪዎች፦
📌በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 56,000 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 44,500 ብር
ለድንበር ተሻጋሪ የጭነት ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 28,500 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 15,200 ብር
ለሕዝብ ታክሲ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 11,700 ብር
📌በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 9,400 ብር
ለከተማና የሀገር አቋራጭ አውቶቡስ፣ ለመንግሥት፣ ለአካል ጉዳተኛ (PD) እና ለባለሦስት እግር (ባጃጅ) ተሽከርካሪዎች፦
📌በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 9,400 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 7,100 ብር
ለባለሁለት እግር (ሞተርሳይክል) ተሽከርካሪዎች፦
📌 በነዳጅ የሚሰሩ ከሆነ፦ 4,700 ብር
📌 በኤሌክትሪክ እና በተፈጥሮ ጋዝ የሚሰሩ ከሆነ፦ 3,550 ብር ሆኗል።

🖋️ በጫካ ውስጥ "ባሩንዳ" የሚባል ሁለት ራስ ግን አንድ አካልና አንድ ሆድ ያለው ወፍ ነበር። የቀኙ ራስ አስተዋይና ታጋሽ ሲሆን፣ ግራ ኛው ራስ ደግሞ ምቀኛና ቶሎ የሚቆጣ ነበር።አንድ ቀን...
11/06/2026

🖋️ በጫካ ውስጥ "ባሩንዳ" የሚባል ሁለት ራስ ግን አንድ አካልና አንድ ሆድ ያለው ወፍ ነበር። የቀኙ ራስ አስተዋይና ታጋሽ ሲሆን፣ ግራ ኛው ራስ ደግሞ ምቀኛና ቶሎ የሚቆጣ ነበር።
አንድ ቀን ቀኙ ራስ በጣም አንድ ጣፋጭ ፍሬ አግኝቶ በልቶ ፍሬው በጣም ጣፋጭ እንደነበረ ይናገራል።ይህንን የሰማው የግራ ኛው ራስ በቅናት 'እንዴት አላካፈልከኝም ከመዋጥህ በፊት?'። ብሎ ቀኙ ላይ ጮኸበት። ቀኙ ራስ "ወንድሜ እኔ ብበላው ወይም አንተ ብትበላው ምን ልዩነት አለው? ሆዳችን እኮ አንድ ነው፣ ለአንተም ይጠቅማል" አለው። ግራው ሊሰማው አልቻለም። በጥላቻ ተሞልቶ በቀልን ያጠነጥን ጀመር።
ከጥቂት ቀናት በኋላ፣ የግራ ኛው ራስ መሬት ላይ መርዛማ ፍሬ ያያል። "ይህንን መርዝ በልቼ ያንን ቀኝ ኛውን ራስ እገድለዋለሁ!" ብሎ ይነሳል።
ቀኙ ራስ እየለመነው "እባክህ እንዳታደርገው! መርዙን ከበላኸው የምንሞተው ሁለታችንም ነን!" እያለ ቢጮኽም፣ የግራ ኛው ራስ ግን መርዙን ዋጠው።
ብዙም ሳይቆይ መርዙ በአንድ አካላቸው ውስጥ ተሰራጭቶ ሁለቱም ራሶች በስቃይ ህይወታቸው አለፈች።
በቤተሰብ፣ በማህበረሰብም ሆነ በሀገር ደረጃ ሁላችንም የተለያየ ሃሳብ (ሁለት ራስ) ቢኖረን፤ የምንጋራው ህይወት ግን አንድ አካል ነው።
ሌላውን ለመጉዳት የምንረጨው መርዝ፣ በመጨረሻ እኛኑ መልሶ ያጠፋናል።ሌላው ሲጠፋ አብረን እንደምንጠፋ ካወቅን፣ ጥላቻን ትተን በፍቅር መኖር እንጀምራለን። ፍትህ በአርሲ ለሞቱት ወገኖቻችን ‼️

‼️ ወንጀለኛን ማበረታታት ነው የያዛችሁት ወይስ ከምር ይሄ ቅጣት ያስተምራል ብላችሁ ነው የሞት ፍርድ የሚገባውን ሰውዬ እንደዚህ በ ሞች ቤተሰብ ላይ አና በተደፈርች ሴት ልጁ ላይ የምትቀልዱ...
10/06/2026

‼️ ወንጀለኛን ማበረታታት ነው የያዛችሁት ወይስ ከምር ይሄ ቅጣት ያስተምራል ብላችሁ ነው የሞት ፍርድ የሚገባውን ሰውዬ እንደዚህ በ ሞች ቤተሰብ ላይ አና በተደፈርች ሴት ልጁ ላይ የምትቀልዱት ያሳዝናል በውነት::

👉 ነገሩ እንደት ነው? አባቷን ገድሎ ልጅቱን የደፈረው ተከሳሽ በ16 ዓመት ከ6 ወር መቀጣቱን ሠምተናል።

ተከሳሽ ፍታለው አሰበው ከስድስት ግብር አበሮቹ ጋር በመሆን ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም በአዳኝ አገር ወረዳ ጫቆ ወረዳ ጫቆ ቀበሌ ልዩ ቦታው ገዳም ሰፈር ተብሎ በሚጠራው ቦታ አድሴ ደጉ የተባለን ግለሰብ ላይ የግድያ ወንጀል በመፈፀም እና የሟችን ልጅ በመደፈር ከግብረ አበሮች ጋር ተሰውሮ ቆይቷል።

በተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀስ ቆይቶ የካቲት 06 ቀን 2017 ዓ/ም መተማ ወረዳ አኩሸራ ቀበሌ ልዩ ቦታው ገነተ ማሪያም በሚባል ቦታ በፀጥታ ሃይል ተይዞ ፖሊስ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ለምዕራብ ጎንደር ዞን ዓ/ህግ መዝገቡን በመላክ ክስ ተመስርቷል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን ከፍተኛው ፍርድ ቤት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችን ወንጀል ከመፈጸም እንዲቆጠቡ ያደርጋል ፤ ያስተምራል ያለውን በአስራ ስድስት ዓመት ከስድስት ወር ፅኑ እስራት እና በአንድ ሽህ ብር በመቅጣት ውሳኔ ማሳለፉን የገንደውሃ ኮሙኒኬሽን ዘግቦ ተመልክተናል።
Via-WasuMohammed

ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከስራ ሊታገዱ ነው‼​ በአዲስ አበባ ከተማ በሚንቀሳቀሱ የታክሲ አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች ላይ አዲስና ጥብቅ መመሪያ መውጣቱን የከተማዋ ትራን...
10/06/2026

ከታሪፍ በላይ የሚያስከፍሉ የታክሲ አሽከርካሪዎች ከስራ ሊታገዱ ነው‼

በአዲስ አበባ ከተማ በሚንቀሳቀሱ የታክሲ አሽከርካሪዎችና ተሳፋሪዎች ላይ አዲስና ጥብቅ መመሪያ መውጣቱን የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ።

በዚህም መሰረት ህግ በሚጥሱ አሽከርካሪዎች ላይ የእገዳ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።

​እንደ ቢሮው ማብራሪያ፥ ከዚህ በኋላ ከተፈቀደው ታሪፍ በላይ ትርፍ ስራ የሚያስከፍሉ አሽከርካሪዎች ላይ አዲስ የእርምጃ ስልት ተዘርግቷል።

ማንኛውም አሽከርካሪ ከተቀመጠው ታሪፍ በላይ ዋጋ አስከፍሎ ሶስት ጊዜ በተደጋጋሚ ጥቆማ ወይም ክስ ከቀረበበት፥ ከትራንስፖርት አገልግሎት ስራው ሙሉ በሙሉ የሚታገድ ይሆናል።

​ይህ አዲስ መመሪያ የወጣው ባለፈው የግንቦት ወር ብቻ ከታሪፍ በላይ በማስከፈልና ተገቢ ያልሆነ የታሪፍ ዝርዝር በመተግበር ዙሪያ ከህብረተሰቡ የቀረቡትን በርካታ ቅሬታዎች ተከትሎ መሆኑ ታውቋል።

🖋️ የዓለም ዋንጫ ደረሰም አይደል እስኪ ስለ ጃፓኑ ዛዮን ሱዙኪ (Zion Suzuki) የግድ ማውራት አለብን.. 🫡🇯🇵🧤⬇️ግማሽ ጋናዊ ሆኖ በጃፓን ያደገው ግብ ጠባቂው ዛዮን ሱዙኪ፣ ሁልጊዜም...
09/06/2026

🖋️ የዓለም ዋንጫ ደረሰም አይደል እስኪ ስለ ጃፓኑ ዛዮን ሱዙኪ (Zion Suzuki) የግድ ማውራት አለብን.. 🫡🇯🇵🧤⬇️

ግማሽ ጋናዊ ሆኖ በጃፓን ያደገው ግብ ጠባቂው ዛዮን ሱዙኪ፣ ሁልጊዜም ቢሆን ከሌሎች የተለየ ነበር። ገና ከትንሽነቱ ጀምሮ ጎልቶ ይታይ የነበረ ሲሆን፣ ከዚህም ጋር ተያይዞ አብዛኞቹ ወጣት ተጫዋቾች ተጋፍጠውት የማያውቁት ከፍተኛ ትኩረት፣ ጫና እና የሰላ ትችት ያሳልፍ ነበር።

እንደ አንድ ግብ ጠባቂ፣ እያንዳንዱ የምትሰራው ስህተት በትልቁ ነው የሚታየው። እያንዳንዱ ስህተት የጋዜጣ አርዕስት ይሆናል። እያንዳንዱን ከባድ ግዜያት ደግሞ ለመደበቅ የማይቻል ነው።

በኡራዋ ሬድ ዳይመንድስ (Urawa Red Diamonds) ክለብ እያለ፣ ሱዙኪ ገና በለጋ እድሜው ነበር በፍጥነት ወደ ዋናው ቡድን እንዲያድግ የተደረገው። ብቃቱ ግልጽ የነበረውን ያህል፣ ከእሱ የሚጠበቀው ነገርም እንዲሁ ከባድ ነበር። የተጫዋቾች አቋም መውረድ ሲጀምር፣ የሚሰነዘረው ትችት እጅግ ከባድ ነበር። ስለ ብቃቱ፣ ስለወደፊት እጣ ፈንታው እና እንዲያውም በከፍተኛው የእግር ኳስ ደረጃ ላይ ለመጫወት ብቁ ስለመሆኑ ጥያቄዎች ይነሱ ነበር።

ብዙ ወጣት ተጫዋቾች በዚህ ጫና ውስጥ ይሰባበሩ ነበር። እሱ ግን ከባድ የሆነውን መንገድ መረጠ። 💪🔥

ሱዙኪ የሀገሩን ምቾት ትቶ ወደ ቤልጂየሙ ሲንት-ትሩይደን (Sint-Truiden) አመራ፤ ስም ምንም ቦታ ወደሌለውና ብቃት ብቻ ዋጋ ወደሚሰጥበት፣ ይበልጥ ፈጣን፣ አካላዊ ብቃትን ወደሚጠይቅና ምህረት ወደሌለው አዲስ አካባቢ ተሻገረ።

ሽግግሩ ቀላል አልነበረም። ስህተቶች ተከስተዋል። ተጠራጣሪዎቹም ድምፃቸውን ከፍ አደረጉ። እሱ ግን እምነቱን መቼም አላጣም። ሰራ። ተማረ። እራሱንም አሻሻለ።

ከሁሉም በላይ ደግሞ፣ አንድ ታላቅ ግብ ጠባቂ ለመሆን የሚያስፈልገውን ጠንካራ ስነ-ልቦና ገነባ፤ ከውድቀቶች በኋላ መልሶ የማገገም እና ጫናው በበረታበት ሰዓት ምርጥ ብቃትን የማሳየት ችሎታን አዳበረ። 🧠🧱

ዛሬ ሱዙኪ የጃፓን ቁጥር 1 ግብ ጠባቂ የሆነው በይሉኝታ ወይም በወሬ አይደለም። የጃፓን ቁጥር 1 የሆነው በራሱ ጥረት ስላረጋገጠው ነው። ብዙዎችን ሊሰብሩ የሚችሉ አስቸጋሪ ጊዜያትን አልፎ እዚህ ደርሷል።

ባለፈው የኢንተርናሽናል ጨዋታዎች እረፍት ወቅት፣ በእንግሊዝ ላይ መረቡን ሳያስደፍር (Clean sheet) በመውጣት ሌላ ታሪካዊ ብቃቱን አሳይቷል፤ እንዲሁም ጃፓን የሶስቱ አንበሶችን (እንግሊዝን) ያሸነፈች የመጀመሪያዋ የእስያ ሀገር እንድትሆን ታሪክ ሰርቷል። 🏆🇯🇵👏

ገና በ23 ዓመቱ በአለም እግር ኳስ ውስጥ ካሉ እጅግ ተስፋ ሰጪ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ላይም የጃፓን የመጀመሪያ ተመራጭ ግብ ጠባቂ ለመሆን ተዘጋጅቷል። 🌎🏆🧤

አሁን እየተመለከትን ያለነው አንድ ጎበዝ ግብ ጠባቂ ወደ ጫፍ ሲደርስ ብቻ አይደለም። ይህ ታሪክ ለእያንዳንዱ ጥርጣሬ መልስ የሰጠ፣ እያንዳንዱን ተቺ ዝም ያሰኘ እና እያንዳንዱን ውድቀት ወደ ስኬት ማገዶነት የቀየረ ተጫዋች ታሪክ ነው። 🔥

ይህ ዝም ብሎ ማደግ ብቻ አይደለም። ይህ ለተቺዎቹ የተሰጠ ታላቅ ምላሽ ነው! 🇯🇵🧱✨
Via-Essa ibnu Rukia

ለጥንቃቄ ተጠቀሙበት‼ ድርጊቱ ያሳዝናል‼📌ለሌሎችም ሼር በማድረግ ንገሯቸው።ይህ ወንድማችን ሚኒሊክብርሀኑ ይባላል፣ከቤተሰቡ ከጠፋ 2ዓመት አልፎታል!የተጨነቀች እህቱ "እባካችሁን ወንድሜ ጠፍቶ ...
07/06/2026

ለጥንቃቄ ተጠቀሙበት‼ ድርጊቱ ያሳዝናል‼

📌ለሌሎችም ሼር በማድረግ ንገሯቸው።

ይህ ወንድማችን ሚኒሊክብርሀኑ ይባላል፣ከቤተሰቡ ከጠፋ 2ዓመት አልፎታል!የተጨነቀች እህቱ "እባካችሁን ወንድሜ ጠፍቶ ቀረብኝ ዛሬ ደግሞ ልደቱ ነበር እናት አባቱም እያለቀሱ ነው አግዙኝ"ብላ በፌስቡክ ለጥፈነው እናንተ ደጋጎችን አስቸግረን ነበር፣

ትላንት አንድ ኮማንደር ነኝ የሚል ሰው በተቀመጠው የእህቱ ስልክ ደውሎ" ትክክለኛ እህቱ ነሽ?እስካሁንስ የት ሄዳችሁ ነው?ልጁ እኮ ጭንቅላቱን በጥይት ተመቶ በአፋር ክልል ወታደራዊ ካምፕ ተኝቶ ነው የሚገኘው፣ፎቶውን እልክልሻለሁ፣ብታይው ታውቂዋለሽ ወይ?ብሎ ጠየቃት!አዎ ወንድሜ አደል አለችው!

በፍጥነት Edit ተደርጎ የታመመ ሰው ፎቶ ልኮላት የተጨነቀች እህት ስታየው እውነትም ወንድሟ ሚኒሊክ መስሏት እንኳን በህይወት ኖረልኝ"ምንድነው ማድረግ ያለብኝ?"ብላ ጠየቀችው፣

አንቺ ተረጋጊ መቀበል ከቻልሽ ሹፌር አመቻችና ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እልክልሻለሁ፣ብሎ የተባባሪውን የሹፌር ስልክ ላከላት!

ምስኪን እህት ፅዮን ሹፌሩ የተባለው ጋር ደውላ አወሩ፣አይዞሸ እኔም ወንድ ልጅ አይደለሁ፣መውደቂያዬን አላውቅም፣ለራሴ ስል ነው መልካም ማደርገው፣አላት፣የነዳጅ 8000ብር ላከችለት፣ወደ አዲስ አበባ እስኪመጣ ኦክስጅኑ መነቀል ስለማይችል ተመላሽ የሚሆን ማስያዣ 23500 ይፈልጋሉ ብሏት በድጋሚ ላከችለት፣አድራሻዋን ጠየቃት ስደርስ እደውላለው አላት፣

ትላንት ቀኑን ሙሉ በጉጉትና በተስፋ ጠበቀችው፣በየመሀሉ ስትደወልለት እዚህ ደርሻለው እያለ ተስፋ ሰጥቷታል፣ ሲመሽ አሁንስ ወንድሜ የት ደረስክ ስትለው መተሀራ ነኝ ተዘጋጂ ብሏታል!

ቶሎ በመድረሱ ገርሟታል፣ቀኑን ሙሉ እያለቀሰች ለአመታት ድምፁ እንኳ የናፈቃት ወንድሟን ለማየት ጓጉታለች፣ "አይኑ ግን ያያል?ብላ ደጋግማ ጠይቃለች!እስክትዳብሰው ጓጉታለች!!

ሰዓታት ሄዱ ቀኑን ሙሉ ስትደውልለት የነበረው ሹፌር ስልኩ ዝግ ሆነ፣ኮማንደር የተባለው ጋርም ስትደውል "ጥሪ አይቀበልም" አላት፣ ደነገጠች ስታሰላስል እንደተጫወቱባት ተረዳች፣ወደ ፖሊስ አመራች፣ "ሸውደውሻል ሌቦች ናቸው" አመልክቺ አሏት!!

በሰው ህይወት የሚጫወቱ አረ መ ኔዎችን ህጉ እንዴት ይሆን የሚቀጣቸው?ከመስረቃቸው የሚሄዱበት የወንጀሉ ርቀት አስቡት እስኪ😭 በውሸት በተቀነባበረ ፎቶ እንዲህ ሆኖ ሲያዩ ሌላ የሚጎዳ እናት አባት ቤተሰብ አለ እኮ፣ እንዴትስ ነው የሚያስችላችሁ? እባካችሁን ሌሎቻትሁ ተጠንቀቁ‼️

እህቱ ፅዮን "ከኔ ተማሩ ከወንጀለኞች ራሳችሁን ጠብቁ🙏 "ብላችኋለች!እናንተም መረጃው ለብዙዎች እንዲደርስ ሌላ ሰው እንዳይሸወድ #ሼር አድርጉ🙏 ለምታውቁት ሁሉ አሳውቁ‼️
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም-ባይሽ ኮልፌ

የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ‼እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ ሐሙስ ዕለት የዓለም የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል። ስምምነቱ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ቀጣናዊ ው...
04/06/2026

የነዳጅ ዋጋን ቀነሰ‼

እስራኤል እና ሊባኖስ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ተከትሎ ሐሙስ ዕለት የዓለም የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ስምምነቱ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ቀጣናዊ ውጥረት ያረግባል እንዲሁም የዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት ስጋትን ይቀንሳል የሚል ተስፋ ጥሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ዓለም አቀፉ የኢነርጂ ኤጀንሲ (IEA) አሁን ያለው የነዳጅ ክምችት መቀነስ ከቀጠለ፣ ፍላጎት በሚጨምርበት የክረምት ወቅት የዓለም አቀፍ ክምችት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ሊደርስ እንደሚችል አስጠንቅቋል

እኛ ሀገርስ ይቀንሳል ወይ ነው ጥያቂው 🤔

03/06/2026

🖋️ እንግዲ ምንም ማድረግ አይቻልም አንደርሰን ወደ ማንቼ ሳብ ተብሏል አሉ አስቲ ይሄን ጎል አይታችሁ መስክሩ ልጁ ብቃት አለው ወይስ ያለውም

01/06/2026

የ አደባባይ ዝርፊያ ‼️

🖋️ እንደው ሰው አይደላችሁም ምን አደርግ ነው የምትሉት ይሄን ሕዝብ ቆይ ከ ሃገሩ ውቺ ወዴት ይሂድ
👉 አረ የመንግስት ያለ እያለ አኮ ነው ህዝቡ አረ ግፍ ነው ቢያንስ ቢያንስ ትንሽ ህሊና ይኑራችሁ አንጂ
👉 ስንት ዓመት በርሃ ለበርሃ ሲነዳ እና ቤተሰቡን ሲረዳ የነበረ ሹፌር ና ከ የልጆችህን ጉሮሮ ዘግተን አኛ እንብላ ማለት ግፍ አይሆንም
👉 እንኩአን ሹፌር ሊላ ሥራ የሚሰራው ሕዝብ ኑሮ ከብዶታል ለ ቤተሰቡ ብሎ አኮ ነው ሞት አንዳለ እያወቀ እራሱ በበርሃ የሚሰቃየው
👉 እንደው ትንሽ አታፍሩም ሕግ የለም ባገሩ አረ እንደዚህ አይደረግም የሚል ትልቅ ሰው ይጥፋ መሀላችሁ
👉 አረ ስለ ወንድ ልጅ አምላክ ብላችሁ ቢያንስ ሕዝብ ለመዝረፍ ምክንያታችሁ ይመር
👉 እንደው ስልጣን ስላለ ብቻ ቁርስ በልቶ ምሳ መድገም ያቃተው ሕዝብ ላይ አንደዚህ መሆን ልክ አይደለም
👉 እስቲ ከ ደሃ ዘርፋችሁ ሳይሆን በሊላ ነገር ሃብታም ለመሆን ሞክሩ
👉 እንዴ አረ የመንግስት ያለ ! አረ የ ሕግ ያለ ! እረፉ ግፍ ነው እረፉ ኃጢያት ነው እረፉ እረፉ እረፉ.....😔
👉 ይሄን ለማሰብ ሰው መሆን በቂ እኮ ነው እኔ የምለው እንደናን ተ ጥሬ ስጋ ሳይሆን ሽሮ በልቶ እራሱ ቁርሱን በልቶ ምሳውን መድገም አቅቶታል እይልኩህ አኮ ነው
👉 እረፉ እረፉ እረፉ........ 😔
Share share ‼️

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Liveaddis-ላይቭ አዲስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Liveaddis-ላይቭ አዲስ:

Share

Category