Liveaddis-ላይቭ አዲስ

Liveaddis-ላይቭ አዲስ We take care of your hassle and minimize your budget and you focus on your business.

Events and Entertainment
Live Addis Events and Entertainment organizes flawless events carefully and professionally designed based on your specific needs and wants. ምን ዓይነት ፕሮግራም ለማዘጋጀት አስበዋል? ላይቭ አዲስ ኢቭንት የእርሶን ፍላጎት ፣ በጀት እና ጊዜ ታሳቢ በማድረግ ከሚያስቡት በላይ ያማረ እና የተሳካ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት የታወቀ ኢቭንት አዘጋጅ ድርጅት ነው፡፡ እርስዎ ስራዎ ላይ ትኩረት ያድረጉ እኛ ከ ሀ እስከ ፐ ያለውን የፕሮግራሙዎን ጣጣ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ብቃት ባላቸው ባለሞያዎች ጥንቅቅ አድርገን መስራት

ብቻ ሳይሆን ወጪዎን ጭምር በመቀነስ ከጭንቀት እና ውጥረት እንገላግሎታለን፡፡ ለማንኛውም ፕሮግራም ላይቭ አዲስ ኢቭንትን ያማክሩ፡፡ ለሠርግ ፣ ለልደት ፣ ለሙዚቃ ኮንሰርት ፣ ለምርቃት ፣ ለቤቢ ሻወር ፣ ወዘተ ላይቭ አዲስ ኢቨንት ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡ ምን እያሳሰቦት ነው? ዲኮር ፣ ዲጄ ፣ ላይቭ ባንድ ፣ ታዋቂ እና ዝነኛ ዘፋኞች ማግኘት ፣ የተዋበ አዳራሽ ፣ ተወዛዋዥ ፣ አጃቢ ፣ ባህላዊ አልባሳት ፣ ... ላይቭ አዲስ ኢቭንት ሁሉም ፍላጎትዎን በዝርዝር እና በጥንቃቄ ተረድቶ ለእርሶ በሚመጥን ደረጃ ያዘጋጅሎታል፡፡

🖋️ አርቲስት ግሩም በተለያዩ ክለቦች ሲሰራ የምናቀው ወንድማችን ሲሆን በተለይ ደሞ የ ጥላሁን ዘፋኝ በመሆን ያስመሰከረ ወንድማችን ነበር ባደረበት ህመም ከዚ ዓለም ድካም አርፏል ለ ወንድማች...
13/08/2026

🖋️ አርቲስት ግሩም በተለያዩ ክለቦች ሲሰራ የምናቀው ወንድማችን ሲሆን በተለይ ደሞ የ ጥላሁን ዘፋኝ በመሆን ያስመሰከረ ወንድማችን ነበር ባደረበት ህመም ከዚ ዓለም ድካም አርፏል ለ ወንድማችን ነብስ ይማር አያልን ለ ቤተሰቦቹ እና ጉደኞቹ መፅናናትን እንመኛለን 😔

ይቺ ወጥመድ የሆነች ዓለም 😔
07/08/2026

ይቺ ወጥመድ የሆነች ዓለም 😔

ለትውስታ ያክል 😆 እና ምን ለማለት ነው ሊጉ አይጀመርም ወይ ⚽
06/08/2026

ለትውስታ ያክል 😆
እና ምን ለማለት ነው ሊጉ አይጀመርም ወይ ⚽

31/07/2026

እሺ አሁን የት እንግባ 🙆‍♂️😆

ኢትዮጵያ 55% ሴቶች "ባል ሚስቱን መደብደብ አሳማኝ ምክንያት ሊኖረው ይችላል" ብለው እንደሚያምኑ ተገለጸ​በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና አጋሮቹ በተካሄደው አገር አቀፍ የዴሞግራፊና ጤ...
30/07/2026

ኢትዮጵያ 55% ሴቶች "ባል ሚስቱን መደብደብ አሳማኝ ምክንያት ሊኖረው ይችላል" ብለው እንደሚያምኑ ተገለጸ

በኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትና አጋሮቹ በተካሄደው አገር አቀፍ የዴሞግራፊና ጤና ዳሰሳ ጥናት፤ 55 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመምታት የሚያስችሉ አሳማኝ ምክንያቶች አሉ ብለው እንደሚያምኑ ይፋ ሆነ።

​በጥናቱ ከተሳተፉት መካከል ይህንን አመለካከት የሚጋሩት የወንዶች ቁጥር 39 በመቶ ሲሆን፣ አብዛኞቹ ምላሽ ሰጪዎች ለምታ በቂ ምክንያት አድርገው የጠቀሱት "ልጆችን ቸል ማለት" የሚለውን ነው።

📌​የለውጥ ሂደት፡ ድብደባውን የሚደግፉ ሴቶች ቁጥር ከ25 ዓመት በፊት ከነበረበት 85 በመቶ አሁን ወደ 55 በመቶ ቢቀንስም፤ የወንዶች ድርሻ ግን ከ10 ዓመት በፊት ከነበረበት 28 በመቶ ወደ 39 በመቶ አድጓል።

📌​የክልልና የትምህርት ልዩነት፡ በሲዳማ ክልል 74% ሴቶች ድብደባውን ሲደግፉ፣ በሶማሌ ክልል ግን 23% ብቻ ነው። በተጨማሪም ያልተማሩ ሴቶች ድብደባውን የመደገፍ እድላቸው (63%) ከተማሩት (29%) በእጅጉ የላቀ ሆኖ ተግኝቷል።
​በጥናቱ መሠረት ባል ወይም አጋር ካላቸው ሴቶች 30 በመቶ ያህሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 58 በመቶ የሚሆኑት ምንም ዓይነት እገዛ አልጠየቁም። የሴቶች መብት ተሟጋቾች ይህንን ጎጂ አመለካከት ለመቀየር የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማሳደግና ሰፊ የግንዛቤ ሥራ መሥራት እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።
Via-wasu Mohammed

28/07/2026

🖋️የኔ አባት አያሳዝኑም በዚ ልክ በ እግዝያብሔር መተማመን አይገርምም 🖤

አቤት ጭካኔ 😔የታመነችው ወዳጅ የሞት ወጥመድ፡ የቅዱሳን ይርጋለም አሰቃቂ የግድያ ሴራና የፖሊስ የምርመራ ውጤትየ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ተወዳዳሪ የሩታ ይርጋለም ታላቅ እህት ቅዱሳን ይ...
28/07/2026

አቤት ጭካኔ 😔

የታመነችው ወዳጅ የሞት ወጥመድ፡ የቅዱሳን ይርጋለም አሰቃቂ የግድያ ሴራና የፖሊስ የምርመራ ውጤት
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ተወዳዳሪ የሩታ ይርጋለም ታላቅ እህት ቅዱሳን ይርጋለም በተፈጸመባት እጅግ አሰቃቂ የእገታና የግድያ ወንጀል ሕይወቷ ማለፉ የመላውን ህዝብና የማህበረሰብ ልብ የሰበረ ክስተት ሆኗል።
በሞደሊንግ ዓለም ስኬትን ለማስመዝገብ በምትተጋው ቅዱሳን ይርጋለም እና ከትምህርት ቤት ጀምሮ በቅርብ የምታውቃት ጓደኛዋ ቅድስት ሙሉቀን መካከል የጠነከረ ወዳጅነት የነበረ ቢሆንም፣ ከጀርባው ግን ምቀኝነትና አደገኛ ሴራ ተሸሽጎ ነበር።
አርብ ዕለት ቅድስት ሙሉቀን ላለፉት ጥቂት ጊዜያት ያልተገናኘችውን ቅዱሳንን በስልክ በመደወል «አዲስ ኮንዶሚኒየም ተከራይቼአለሁ፤ መጥተሽ ቤቴን እዪልኝ፤ ደግሞም የሚያገናኝሽ አዲስ የሥራ ዕድል አለ» በማለት የደስታና የጽኑ ወዳጅነት በሚመስል መንፈስ ጥሪ አቀረበችላት።
ቅዱሳን በጓደኛዋ ላይ አንዳችም ክፋት ሳትጠረጥር ሜክሲኮ አካባቢ ተገናኝተው አብረው ወደ ኮዬ ፈጬ ኮንዶሚኒየም አመሩ።
ኮዬ ፈጬ በሚገኘው አዲስ ኮንዶሚኒየም ደጃፍ ደርሰው ወደ ቤት እንደገቡ፣ ቀድሞ ተደብቆ ይኖር የነበረው የቅድስት ፍቅረኛ ደስአለኝ፣ ቅዱሳን ድምፅ እንኳ አውጥታ እንዳትጮህ አፍኖ በማሰር እገታውን ፈጸመ።
አጋቾቹ ወዲያውኑ ለሟች ቤተሰቦች በመደወል የ2 ሚሊዮን ብር ቤዛ እንዲከፈላቸው ጠየቁ። የቤተሰብ ልብ በጭንቀትና በድንጋጤ ተሞልቶ የገንዘብ ድርድርና ዝግጅት በሚያደርግበት ወቅት፣ አጋቾቹ ቅዱሳን በቅርብ የምታውቃቸው በመሆኑ ነፃ ብትወጣ የፈጸሙትን ምስጢር አሳልፋ እንደምትሰጣቸው ተገነዘቡ።
በዚህም ፍርሃትና ጭካኔ በተሞላበት ውሳኔ፣ በዚያው አርብ ዕለት የቅዱሳንን ሕይወት በአሰቃቂ ሁኔታ አጠፉት።
አስክሬኗንም ማንም እንዳያገኘው በማሰብ እዚያው አካባቢ በተከራዩት ሌላ ተጨማሪ ኮንዶሚኒየም ውስጥ ደበቁት።
ሆኖም አጋቾቹ የፈጸሙት ግፍ በጨለማ ሊቀበር አልቻለም። የፖሊስ አባላት ባደረገው ፈጣንና የተቀናጀ ክትትል፡
1. ዋናኛዋ ተጠርጣሪ ቅድስት ሙሉቀን በአዲስ አበባ ጎተራ አካባቢ በቁጥጥር ስር ዋለች።
2.ተባባሪው ደስ አለኝ ደግሞ ሁኔታዎች ሲከፉበት ለማምለጥ ሞክሮ በአዳማ ከተማ ተደብቆ እያለ በፖሊስ ተያዘ።
በአጠቃላይ ከወንጀሉ ጋር በተያያዘ 8 ሰዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፣ ዋና ዋናዎቹ ተጠርጣሪዎች ወንጀሉን መፈጸማቸውን አምነው ድርጊቱን እንዴት እንደፈጸሙት በቦታው ተገኝተው ለፖሊስ አሳይተዋል።
ይህ አሰቃቂ ድርጊት መላውን ማህበረሰብ ያስቆጣና ያስዘነዘነ ሲሆን፣ እህቷ ሩታ ይርጋለም በልብ ስብራት ሆና፡
«እግዚአብሔር የወደደውን አደረገ፤ ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ...»
በማለት ያስፈረመችው መልእክት የዚህን አሳዛኝ ሁኔታ ጥልቀት የሚያሳይ ሆኗል።
via - z habesha

23/07/2026

👣❤️‍🩹

ጀግና አባት‼ ልጃቸውን በፖሊስ አስይዘው መስክረው አሳሰሩት‼በጂማ ዞን ጮራ ቦቶር ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ለቺሳ ደፋር፣ የ16 ዓመት ልጃቸው የሰረቀውን ሞተር ሳይክል ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት...
23/07/2026

ጀግና አባት‼

ልጃቸውን በፖሊስ አስይዘው መስክረው አሳሰሩት‼

በጂማ ዞን ጮራ ቦቶር ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ለቺሳ ደፋር፣ የ16 ዓመት ልጃቸው የሰረቀውን ሞተር ሳይክል ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠትና ፍርድ ቤት ቀርበው በመመስከር የ3 ዓመት እስራት እንዲፈረድበት በማድረግ አስደናቂና አርአያታዊ የሀቀኝነት ተግባር ፈጽመዋል።

አቶ ለቺሳ ለዚህ ውሳኔያቸው በሰጡት አድናቆት የሚያስቸር ምላሽ፡ «ልጄ ከስህተቱ መማር አለበት፤ ባለሞተሩም ለፍቶ ያፈራውን ሀቅ ማጣት የለበትም» ብለዋል።

የሰው ሀቅ ላለመቀበልና ልጃቸውን በስነ-ስርዓት ለማነጽ አባት ያሳዩት ይህ ቀና ስብዕና እና ለህግ የበላይነት ያሳዩት ታማኝነት በብዙዎች ዘንድ ትልቅ አድናቆትን አትርፎላቸዋል።

ራሷን በሽጉጥ አጠፋች ተባለ‼በትግራይ ክልል ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ በጀግንነቷ የምትታወቀው ወጣቷ እናት ታጋይ ብርኽቲ ተኽላይ፣ መኖሪያ ቤቷን ዘግታ በራሷ ሽጉጥ ህይወቷን ማጥፋቷ ታውቋል። ምንም ...
19/07/2026

ራሷን በሽጉጥ አጠፋች ተባለ‼

በትግራይ ክልል ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ በጀግንነቷ የምትታወቀው ወጣቷ እናት ታጋይ ብርኽቲ ተኽላይ፣ መኖሪያ ቤቷን ዘግታ በራሷ ሽጉጥ ህይወቷን ማጥፋቷ ታውቋል።

ምንም እንኳን ህይወቷን ለማትረፍ ወዲያውኑ ወደ አክሱም ቅድስት ማርያም ሆስፒታል ተወስዳ የነበረ ቢሆንም፣ በህክምና እርዳታ ህይወቷን ማዳን ሳይቻል ቀርቷል።

በዚህ ዓመት ትዳር መስርታ ገና የጨቅላ ህጻን እናት የነበረችው የዚች ወጣት አሳዛኝ ህልፈት በቤተሰብና በወዳጅ ዘመዶቿ ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘንን ፈጥሯል።

የታጋይ ብርኽቲ ተኽላይ የቀብር ሥርዓት ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በትኹል ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ለቤተሰቦቿ መፅናናትን እመኛለሁ
Via-WasuMohammed

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Liveaddis-ላይቭ አዲስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Liveaddis-ላይቭ አዲስ:

Shortcuts

Share

Category