ፋኖ ሚድያ

ፋኖ ሚድያ የማህበረሰባችን ፍላጎት ተቀዳሚ ምርጫ መሆን
(1)

" #አማራውን እርስ በእርሱ ደም አቃብተነዋል"❗(ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ)ሚሊሻ ሆኖ ከፋኖ ቤተሰብ ያልገደለ የለም በተመሳሳይ ፋኖ ሆኖ ከሚሊሻ ቤተሰብ ያልገደለ የለም ። በአማራ ባህል ደግሞ ደም...
12/10/2025

" #አማራውን እርስ በእርሱ ደም አቃብተነዋል"❗

(ኦቦ ሽመልስ አብዲሳ)

ሚሊሻ ሆኖ ከፋኖ ቤተሰብ ያልገደለ የለም በተመሳሳይ ፋኖ ሆኖ ከሚሊሻ ቤተሰብ ያልገደለ የለም ። በአማራ ባህል ደግሞ ደም ሳይመልሱ መቅረት እንደነውር የሚቆጠር ነገር አለ ፣ ስለዚህ አሁን ላይ ዕርስበርስ ለግድያ የሚፈላለጉ ደመኞች ሆነዋል፥ ፋኖን አጥፋልን ብለን የምንለምነው ሚሊሻ አይኖረንም ለራሱ ሲል የራሱን ህይወት ለማትረፍ ሲል ያለምንም ክፍያ ፋኖን ያሳድድልናል።በእንደዚህ አይነት መንገድ እጃችንላይ ያለውን ገንዘብ ለሚሊሻ ከመበተን ድነናል፣ ገንዘቡን ለገዳ ልዩ ኮማንዶ ማሰልጠኛ እና መሳሪያ መግዣ ይውላል። አማራ ከዚህ በሗላ ከነሙሉ ክብሩ በአባገዳ ልጆች ፊት የሚቆምበት ዘመን አብቅቷል ማንም አባከና የሚለው ሰው አይኖርም። ቀደም ብየ እንደነገርኳችሁ አማራ ከዚህ በኋላ እስከምፅዓት ድረስ ምንም አይነት የፖለቲካ ወሳኔ ሰጭነት ሚና እንዳይኖረው አድርገን ሰርተናል አንዳንዶች ይሄን ስንል መታበይ ይመስላቸዋል ነገር ግን ፖለቲካውን የሰራነው ሰዎች ስለምናውቀው ነው። ከእንግዲህ ኦሮሞ ማድረግ ያለበት ስትበድለው ከነበረችው ሚኒሊክ ሰራሽ ሐገር ቁጭ ብሎ ካሳ መቀበል ብቻ ነው። ከኦሮሞ ጋር ሰላም ፈጥሬ እኖራለሁ የሚል አካል ካለ እሱን እንቀበላለን ነገር ግን አካሔዱ የሚሆነው ኦሮሞ በሚወስንለት ማነኛውም ህግና ድንጋጌ ሊመራ እና ሊተዳደር አምኖ ከተቀበለ ብቻ ይሆናል። ይሄን ካልተቀበለ ጥሬ ስጋ እየቀለብን አሰልጥነን ያስቀመጥነው ሰራዊት አለን (የኦሮሚያ ልዩ ሀይል)ፈተን እንለቅበታለን ማለት ነው።

-ሽመልስ አብዲሳ ❗የኦሮሚያ ገዳ ልዩ ኮማንዶ የምርቃት ስነስርዓት ላይ የተናገሩት።

 #ፋኖ fano 🦅 Do not celebrate victory too early because some opponents are unpredictable.Give yourself time
06/06/2025

#ፋኖ fano 🦅 Do not celebrate victory too early because some opponents are unpredictable.
Give yourself time

30/05/2025
የአንድነት ጥቅሙ ይኸው ነው!አፋብኃ ለአምባሳደር ማሲንጋ ጥሪ ፈጣን ምላሽ ሰጥቷል!
23/05/2025

የአንድነት ጥቅሙ ይኸው ነው!
አፋብኃ ለአምባሳደር ማሲንጋ ጥሪ ፈጣን ምላሽ ሰጥቷል!

 #ሰበር ዜና    #ሰበር #የኢትዮጵያ #ከአማራ ክልል ወደ አዲስአበባ የሚደረጉ በረራዎች በኦላይን ቲኪት ተቋርጦ አልቋል በማለት አሰከ 15 ቀንድር ያለው ተቋርጦ አልቋል በማለት 4500ብር ...
13/05/2025

#ሰበር ዜና #ሰበር #የኢትዮጵያ
#ከአማራ ክልል ወደ አዲስአበባ የሚደረጉ በረራዎች በኦላይን ቲኪት ተቋርጦ አልቋል በማለት አሰከ 15 ቀንድር ያለው ተቋርጦ አልቋል በማለት 4500ብር ትራንስፖርት የነበረው በረራ ለአነድ በረራ10000ሺህ ብር በህገወጥ አየተሸጠነው ሙስና የተንሰራፋበት የአማራክልል የኢትዮጵያ አየርመንገድ በጠራራ ፀሀይ ዘረፋ ላይ የተሰማሩ ሰራተኞች እና ደዳሎች ህዝቡን ለከፍተኛ እንግለት እየዳረጉት ይገኛሉ የየብስ ትራንስፖርት በክልሉ ወደ አዲስአበባ ለመግባትም ሆነ ለመውጣት የምንግስት ቅልብ ታጣቂዎች ከጓፂዎን እሰከ ደብረፅጌ በተዘረጋው አጋች ቡድን በተደጋጋሚ የታገቱ 200በላይ ሰዎች እሰካሁን አድራሻቸዎ አልታወቀም ህዝቡ ይህን ፍራቻ በአየር መንገድ ሊጠቀም ቢፈልግም በአየርመንገዱ ውሰጥ የተሰገሰጉ ሆዳም ደላሎች እና የአየር መንገድ ሰራተኞች እየተዘረፈ እየተንገላታ ይገኛል #አዲስሼር

 #ዮሐንስ ቧያሌው እና ክርስቲያን ታደለ  በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመብን አሉ። ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እስረኞች ወደ ማደሪያቸው  ከገቡ በኋላ ከምሽቱ ...
03/05/2025

#ዮሐንስ ቧያሌው እና ክርስቲያን ታደለ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥቃት ተፈፀመብን አሉ።

ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ/ም የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት እስረኞች ወደ ማደሪያቸው ከገቡ በኋላ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ቁልፍ ሰብረው እንዳስወጧቸው እና እስከ ሌሊቱ 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ እንዳሳደሯቸው ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ገለፀዋል።

በተመሳሳይ ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ ፣ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ፣ ፕሮፌሰር መዓረጉ ቢያበይን እና ሲሳይ አውግቸው (ዶ/ር) ይሄው ድርጊት የተፈፀመባቸው መሆኑን አርብ ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ/ም ለፍርድ ቤት አቤቱታ አቅርበዋል።

"ቀይ ቦኔት የጫኑ የፌደራል ፖሊሶች ምሽት 12:00 ሰዓት በሩን በኃይል ከፍተው ከገቡ በኋላ ሁላችንንም እጃችንን ወደ ላይ እንድናደርግ አዘው ሜዳ ላይ በሰልፍ አቁመውን በመሳሪያ ሲያስፈራሩን ነው ያደሩት" ሲሉ ነው ለፍርድ ቤቱ የገለፁት።

"ይህን ድርጊት በቦታው ተገኝተው ያስተባበበሩት የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ የሽብር ወንጀል መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር አዱኛ ረጋሳ እና የፌደራል አቃቢ ሕግ የሽብር እና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች መከላከልና መቆጣጠር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ኢዮሲያድ አበጀ ናቸው" ሲሉ ለችሎቱ አስረድተዋል

"እነዚህ ሁለቱ ዳይሬክተሮች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ውስጥ በርካታ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ከወቅታዊ የአማራ ክልል የፀጥታ መደፍረስ ጋር በማገናኘት የሽብር ወንጀል ልትፈፅሙ አቅዳችኋል በማለት ኢ- ሰብዓዊ ድርጊት እየፈፀሙ ይገኛሉ" ሲሉ ተከሳሾቹ አቤት ብለዋል።

"ቀደም ሲል በምርመራ ወቅት ድብደባ የፈፀሙብን ሁለቱ የመንግስት ሹማምንት ሲሆኑ ከሁለት ዓመት በኋላ የቂሊንጦ ማረሚያ ቤትን አጥር ጥሰው ፣ የተኛንበትን ቤት በር በኃይል ሰብረው እስከ ሌሊት 7:00 ሰዓት ድረስ ሜዳ ላይ አሰልፈውን አሳድረውናል። ሕይዎታችን አደጋ ላይ መሆኑን ሕዝባችን እንዲያውቅልን" ሲሉ አሳስበዋል።

ዮሐንስ ቧያሌው እና ክርስቲያን ታደለ ከአንድ አመት በፊት በአዋሽ አርባ ወታደራዊ እስር ቤት በነበሩበት ወቅተ የከፋ የጤና መታወክ ገጥሟቸው እንደ ነበር ይታወቃል። በመሆኑም ጤናቸው ገና ሳያገግም በድጋሜ ሜዳ ላይ ተሰልፈው እንዲያድሩ መደረጉ ለባሰ የጤና እክል ተጋልጠዋል ሲሉ ምንጮቻችን ለመሠረት ሚዲያ ተናግረዋል ።

የፌደራል ፖሊሶች የማረሚያ ቤቱን አጥር ሰብረው ለምን እንደ ገቡ እና በሽብር የተጠረጠሩ እስረኞችን ለምን ከክፍላቸው አስወጥተው ሜዳ ላይ እንዳሳደሯቸው የታወቀ ነገር የለም ።

የአምሓራ ሥነ ልቡና አማራ ውጊያ ሲገጥምኽ ዐቅምኽ ዐንሶ መሸነፍኽን ካመንኽ አይገድልኽም። ሌላው ቀርቶ ሱሪኽን ሳትታጠቅ አይዋጋኽም።  ከጀርባኽ አይወጋኽም። ዐይን ለዐይን እንጅ እንደ ዱር እ...
09/04/2025

የአምሓራ ሥነ ልቡና

አማራ ውጊያ ሲገጥምኽ ዐቅምኽ ዐንሶ መሸነፍኽን ካመንኽ አይገድልኽም። ሌላው ቀርቶ ሱሪኽን ሳትታጠቅ አይዋጋኽም። ከጀርባኽ አይወጋኽም። ዐይን ለዐይን እንጅ እንደ ዱር እንስሳ በድብቅ አይመጣብኽም፤ ሊወጋኽ ቢመጣ እንኳ እንድትዘጋጅ መጣኹልኽ ብሎ ያስጠነቅቅኻል። እንደ ፈሪ ዱላ በተኛኽበት አይቀጠቅጥኽም። እንደ ድንጉጥ ሌባ ድንገት ሊገድልኽ አይከሰትም። ብልጥ እኾናለኹ ብለኽ ቁማር የምትቆምር ከኾነ ግን ያወቀብኽ ጊዜ የሥራኽን ዋጋ ትስተናገዳለኽ። ሲጀመርም አማራ በሕይወቱ ካልደረስኽበት አይደርስብኽም። በፍቅር ትገዛዋለኽ፣ በትሕትናም ታሸንፈዋለኽ። ልብኽ አብጦ ከተዳፈርኸው ግን አይለቅኽም። አምሓራ በሥነ ልቡናው ከጠንካሮች ጋር እንጅ ከደካሞች ጋር አይገጥምም። አምሓራ በሥነ ልቡናው እንደ ስም አይጠሬዎች ንጹሃን ምስኪኖችን፣ ልጃገረዶችን፣ እናቶችንና ሕፃናትን አይረሽንም። ታጥቀው ሊገድሉት የሚመጡን ግን በቋንቋቸው ያናግራቸዋል።

ዐቅመ ቢሶችን የሚያሰቃዩንና የሚገድሉን ካየን እነርሱ የአማራ ሥነ ልቡና የሌላቸው፣ በምናቸውም አማራ ያልኾኑ መኾናቸውን እናስተውል።
(ልጅ ተድላ መልዓኩ ወረደ)

ዐምሓራ በሚለው ስም ውስጥ ኃይል አለ። ዐምሓራ ማለት ግዑዝ፣ አግዓዚ፣ ነጻ አውጪ፣ ዐርበኛ፣ የዐንበሳ ልብ፣ መንፈሳዊ፣ ነገደ ዮቅጣን፣ የእሥራኤል ዘር፣ ሕምያር፣ ሰበአ፣ የማይበገር ማለት ነ...
27/03/2025

ዐምሓራ በሚለው ስም ውስጥ ኃይል አለ። ዐምሓራ ማለት ግዑዝ፣ አግዓዚ፣ ነጻ አውጪ፣ ዐርበኛ፣ የዐንበሳ ልብ፣ መንፈሳዊ፣ ነገደ ዮቅጣን፣ የእሥራኤል ዘር፣ ሕምያር፣ ሰበአ፣ የማይበገር ማለት ነው።

 *ሰሶ በክብር ለአማራነት የተሰዋው                 የአርበኛ አረጋ ጌታቸው  አጭር የህይወት ታሪክ========================[“ሕያው ሁኖ የሚኖር፣ ሞትንስ የማያይ ሰው ...
21/03/2025

*ሰሶ በክብር ለአማራነት የተሰዋው የአርበኛ አረጋ ጌታቸው አጭር የህይወት ታሪክ
========================

[“ሕያው ሁኖ የሚኖር፣ ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?" መዝሙር 89:48]

አርበኛ አረጋ ጌታቸው ከአባቱ ከአቶ ጌታቸው አምሳሉ እና ከእናቱ ወ/ሮ አበሬ አጣናዉ በቋራ ወረዳ ዛና አቦ ቀበሌ በ1980 ዓም ተወለደ። አርበኛው በወላጆቹ እንክብካቤ አድጎል። አርበኛው ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ከልጅነት በጀግንነት እስከ ተሰዋበት ቀን ድረስ በስነ ምግባሩ የተመሠገነ ለተቸገሩ ደራሽ ነው።

አርበኛው የተዋጣለት ኢንቨስተርም ነጋዴም በስራው ደከመኝ ሰለቸኝ የማያውቅ ቅን ፣ ትሁት፣ ሰው አክባሪ አዛኝና ሩህሩህ ፣ሀይማኖተኛ፣ ለሰው ሁሉ መልካም አሳቢ፣ ታጋሽ፣ ደግ፣ አንደበተ ርቱዕ ነበር::

የቤተሰቡ ሁኔታ በተመለከተ ጋብቻውን በሀገሬው ወግ ባህል መሠረት የፈጸመ ሲሆን ልጆችም አፍርቷል። ለቤተሰቡ ፍቅር የሚሰጥ፣ እጅግ የሚናፈቅ ተወዳጅ አባት ነበር::

የትግል ሁኔታውን በተመለከተ አርበኛው ከልጅነቱ ጀምሮ የኢህአዴግ / ወያኔ አንባገነናዊ አገዛዝን ግፍ የሚፀየፍ ለወገኑ ተቆርቋሪ እምብተኛ ነበር። በ2008 ዓ/ም የህውሃት ቅጥረኛ የሆነው ራሱን የቅማንት ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ቡድን የህውሃትን ተልዕኮ ተቀብሎ በቋራና መተማ ፀረ አማራ ግድያና አፈና መፈፀሙን ተከትሎ አይበገሬ ጓዶቹን በማሰባሰብ ቅስሙን የሰበረ፣ ከዛ በኃላ በመላው አማራ ፀረ ወያኔ የትጥቅ ትግል እንዲፋፋም ከፊት ግንባር ቀደም ሁኖ የመራ እና ያስተባበረ ነው።

አርበኛ እብሪተኛው ወያኔ ሰሜን ዕዝን በማጥቃት አማራን ወረራ መጀመሩን ተከትሎ የአካባቢውን አርበኞች በማስተባበር በወልቃይት ጠገዴ ግንባር በአብራጅራ ግንባር በሎጉዲ ፣ ማይካድራ ፣ ሁመራ ድረስ በጀግንነት ተፋልሞ ህውሃትን ከወልቃይት ጠገዴ ጠለምት ምድር ተጠራርጎ እንዲወጣ የአርበኝነት ግዴታውን የተወጣ ጀግና ነበር።

አርበኛው ህውሃት ለመልሶ ወረራ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ወረራ ሲከፍትም በተለመደ ጀግንነቱ አርበኞችን ከፊት እየመራ እና እያስተባበረ ጨቋኝ ወራሪ አረመኔዋን ህውሃት ተፋልሟታል።

አርበኛ አረጋ ጌታቸው ተረኛው የጦር ወንጀለኛው የኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ይፋዊ ወረራ ከጀመረበት የዛሬ ሁለት ዓመት ጀምሮ በቋራ እና አካባቢው ያለውን የታጠቀ እና ያልታጠቀ ህዝብ በማስተባበር ወረሪውን በመመከት ብሎም በአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ በአሁኑ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር አካል የሆነውን ቋራ ኦሜድላ ክፍለ ጦርን በመመስረት እንዲሁም የተቋሙ ከፍተኛ አመራር በመሆን የህልውና ትግሉን እየመራ የነበረ አርበኛ ነው። አርበኛው በከፍተኛ አመራርነት የሚመራው ቋራ ኦሜድላ ክፍለ ጦር አገዛዙ ቋራና አካባቢውን ለቆ እንዲፈረጥጥ በማድረግ ከአንድ ዓመት በላይ ቀጠናውን በማስተዳደር ረገድ የአንበሳውን ድርሻ የተወጣ ብርቅየ አርበኛ ነው። አርበኛው በትናንትናው ዕለት በጀግንነት እስከተሰዋበት ድረስ በህዝቡ በጦሩ በአመራሩ ተወዳጅ የነበረ መካሪ ዘካሪ ደፋር ህልመኛ፣ ቆስጣና ወታደር ነበር። ከዚህም ባሻገር ለጎንድር አንድነት ከፍተኛ ሚና የነበርዉ ጀግና ታታሪ ፣ አርቆ አሳቢ ፣ ብላሀተኛ ፣ አስታራቂ ነበር አርበኛችን በዋለበት አዉደ ዉጊያ ገሎ እና ማርኮ የሚመጣ የአማራ የቁርጥ ቀን ጀግና ነበር
መቸም ጀግና በትግል ላይ ማረፉ አይቀርም እና ጀግናችን ሞተ ሳይሆን አረፈ ነዉ ።የምንለዉ በመጨረሻም ጀግናችን የጀመረዉን ትግል ለማስቀጠል ቃል እንገባለን ትግልህ ትግላችን ነዉ።
ነብስህ በአፀደ ገነት ፈጣሪ ያኑርል🙏

 #ፋኖ  #የአድዋ ድል በአል ለጥቁሮች በጣም ትልቅ ታሪካዊ እና ምልከታዊ ትርጉም አለው። ይህ ድል በ1896 ዓ.ም. በኢትዮጵያ እና በጣልያን መካከል በተካሄደው የአድዋ ጦርነት ወቅት ተካሄዷ...
01/03/2025

#ፋኖ #የአድዋ ድል በአል ለጥቁሮች በጣም ትልቅ ታሪካዊ እና ምልከታዊ ትርጉም አለው። ይህ ድል በ1896 ዓ.ም. በኢትዮጵያ እና በጣልያን መካከል በተካሄደው የአድዋ ጦርነት ወቅት ተካሄዷል። የኢትዮጵያ ጦር በንጉሠ ነገሥቱ ዳግማዊ ምኒልክ እና በንግሥት �ይቱ ተርጎም እንዲሁም በሌሎች የኢትዮጵያ አመራሮች አምባገነንነት ምክንያት ድል ተቀዳጅቷል።

ይህ ድል ለጥቁሮች በአጠቃላይ እና ለአፍሪካውያን በተለይ ትልቅ ትርጉም አለው ምክንያቱም፡

1. **የአፍሪካ ነፃነት ምልክት**
የአድዋ ድል የአፍሪካ ሕዝቦች በአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት ስር ለመውደቅ እንደማይችሉ የሚያሳይ የመጀመሪያው ትልቅ ድል ነበር። ይህ ድል ለሌሎች አፍሪካውያን ሕዝቦች ነፃነት እንደሚቻል የሚያሳይ ምሳሌ ሆኖ አገልግሏል።

2. **የኢትዮጵያ ነፃነት መጠበቅ**
�ድሉ ኢትዮጵያ ከአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት ነፃ እንድትቀጥል አስችሏታል። ይህ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ውስጥ እንደ ነፃ እና አርቆ የቆመች አገር አስቀምጧል።

3. **የጥቁሮች ኩራት እና ራስን መተማመን**
የአድዋ ድል ጥቁሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ራሳቸውን ማስከበር እና ራሳቸውን መተማመን እንደሚችሉ የሚያሳይ ምሳሌ ሆኖ አገልግሏል። ይህ ድል በጥቁሮች ዘንድ ኩራት እና ራስን መተማመንን አስጨስሯል።

4. **የታሪክ እና የባህል ምልክት**
የአድዋ ድል በኢትዮጵያ ታሪክ እና ባህል ውስጥ እንደ ትልቅ ምልክት ቆሟል። ይህ ድል በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እንደ �ድል እና ኩራት ቀን ይከበራል።

በአጠቃላይ፣ የአድዋ ድል በአል ለጥቁሮች እና ለአፍሪካውያን የነፃነት፣ የኩራት እና የራስን መተማመን ምልክት ሆኖ አገልግሏል።

Address

መነሻውን የሚያውቅ መዳረሻው አይዘነጋም
Addis Ababa
ተረትያስተማረበቅኔታረመ

Opening Hours

Monday 09:00 - 02:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ፋኖ ሚድያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category