26/07/2026
ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ 2026 ሩታ ይርጋለም ታላቅ እህቷን አጣች — ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል
ኦፊሴላዊ የፕሬስ መግለጫ
MISS WORLD ETHIOPIA ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ
በ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊነት ተመርጣ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፉ የሚስ ወርልድ ውድድር ለመወከል በዝግጅት ላይ የነበረችው ሞዴል ሩታ ይርጋለም፣ በተጨማሪም የባህልና ስፖርት የክብር አምባሳደር በመሆን በመላው ኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች እየተዘዋወረች የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝም እና ሀገራዊ እሴቶች በማስተዋወቅ ላይ ትገኝ ነበር።
በዚህ ወቅት የታላቅ እህቷ ቅዱሳን ይርጋለም አሳዛኝ ህልፈት በመከሰቱ ምክንያት የነበራትን ሀገራዊ ተልዕኮ ለጊዜው አቋርጣ ወደ ቤተሰቧ ለመመለስ ተገዳለች።
በፖሊስ በተሰጠው መረጃ መሠረት፣ በጉዳዩ ላይ የተካሄደውን ሰፊ የምርመራ ሂደት ተከትሎ በወንጀሉ ተጠርጥረው የነበሩ ግለሰቦች ከህግ ለማምለጥ ሲሞክሩ፣ በአዲስ አበባ ፖሊስና በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ የተቀናጀ የጋራ ኦፕሬሽን ተይዘዋል።
የቀረው የምርመራ ሂደትም በመቀጠል ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በዚህ አጋጣሚ በምርመራው እና በተጠርጣሪዎች መያዝ ሂደት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
ለሟች ቅዱሳን ይርጋለም ዘላለማዊ ዕረፍትን እንመኛለን፤ ለ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊ ሩታ ይርጋለም፣ ለመላው ቤተሰቧ እና ለወዳጆቻቸው ጥልቅ ሀዘናችንንና ልባዊ ማጽናኛችንን እንገልጻለን ;;
የሟች ቅዱሳን ይርጋለም የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በቤተል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተከናውኗል።
Via ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አዘጋጅ ኮሚቴ